Tuesday, 29 July 2014

41 አለማቀፍ ድርጅቶች የታሰሩት ጋዜጠኞችና ጦማርያን በአፋጣኝ እንዲፈቱ ጠየቁ

  •  

ESAT Daily News Amsterdam July 28 2014 Ethiopia | ESATTUBE

ESAT Daily News Amsterdam July 28 2014 Ethiopia | ESATTUBE

ESAT Eneweyaya July 28, 2014 Ethiopia | ESATTUBE

ESAT Eneweyaya July 28, 2014 Ethiopia | ESATTUBE

Friday, 25 July 2014

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ደብረዘይት አየር ሃይል ግቢ ታስረው ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው ነው


July25/2014
ሐምሌ ፲፰ (አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከሰኔ 18 ቀን 2006 ዓም ጀምሮ ደብረዘይት በሚገኘው የአየር ሃይል ግቢ ውስጥበአንድ አነስተኛ ክፍል ውስጥ ታስረው ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።

ኢሳት የተለያዩ ምንጮችን አነጋግሮ ባሰባሰበው መረጃ አቶ አንዳርጋቸው በመጀመሪያዎቹ 10 ቀናት ከፍተኛ ድብደባ ከተፈጸመባቸው በሁዋላ ድበደባው ቆሞ፣ የማሰቃያ መርፌዎችን እየተወጉና በኤልክትሪክ ሾክ እየተሰቃዩ መረጃ እንዲያወጡ እየተገደዱ ነው።

መርማሪዎች ከአቶ አንዳርጋቸው የሚፈልጉት መረጃ ከግንቦት7 ጋር በጋራ የሚሰሩ  አሁን በስልጣን ላይ ያሉ የኢህአዴግን አመራሮችን እንዲሁም በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያሉ አዛዦችን ስሞች ሲሆን፣ አቶ አንዳርጋቸው ግን እስካሁን ምንም አይነት መረጃ ባለመስጠታቸው ፣ መርማሪዎች ሲበሳጩ መታየታቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ለወትሮው አንድ መረጃ ሲያገኙ በታላቅ ደስታ የሚፈነጩት መርማሪዎች፣ ምርመራቸውን ጨርሰው ሲወጡ የሚያሳዩት ብስጭት፣ እስካሁን ድረስ የሚፈልጉትን እንዳላገኙ የሚያሳይ መሆኑን ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ምንጮች ገልጸዋል።

አቶ አንዳርጋቸው እንዳስፈላጊነቱ በቀን ሶስት ጊዜ ምርመራ እንደሚካሄድባቸው የሚናገሩት ምንጮች፣ ምርመራውን የሚያካሂዱት የተመረጡ የህወሃት የደህንነት ሰራተኞች መሆናቸውንና በግቢው ለበረራ የሚሰለጥኑ የሌሎች ብሄር ተወላጆች ወይም የደህንነት ሰራተኞች ወደ አካባቢው እንደማይሄዱ ገልጸዋል። ምሽት አካባቢ የሚሰማው የጣር ድምጽ የሚረብሻቸው የእለት ተረኛ ጠባቂ መኮንኖች በሁኔታው እያዘኑ አንዳንዶች ስሜታቸውን መቆጣጠር እንደማይችሉ ምንጮች አክለው ገልጸዋል።

ስለ አቶ አንዳርጋቸው የእለት ውሎ ማወቂያ ብቸኛው ዘዴ የመርማሪዎች ፊት ነው የሚሉት ምንጮች፣ እስካሁን ድረስ ምርመራ በሚያካሂዱ የህወሃት አመራሮች  ዘንድ የደስታ ፊት እንደማይነበብ ገልጸዋል።

የኢህአዴግ መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የታሰሩበትን ቦታ ይፋ ለማድረግ እስካሁን ፈቃደኛ አልሆነም። የእንግሊዝ ባለስልጣናት ለአቶ አንዳርጋቸው የኮንሱላር የማማከር አገልግሎት ለመስጠት ጥያቄ ቢያቀርቡም ኢህአዴግ ባለስልጣናት ፈቃደኛ አልሆኑም።

ከዚህ በተቃራኒ ኢህአዴግ በአቶ አንዳርጋቸው እና በግንቦት7 ላይ ለሚሰራው ድራማ ግብአት ይሆን ዘነድ የተለያዩ ሰዎችን ማሰማራቱን ምንጮች ገልጸዋል። ቀደም ብለው በአገዛዙ ለስለላ ወደ ኤርትራ ተልከው እና ለተወሰኑ ወራት ግንቦት7 ትን ተቀላቅለው በመጨረሻ የኢህአዴግ የስለላ አባላት መሆናቸው ሲታወቅ የጠፉ እንዲሁም ፈንጅ ሊያፈነዱ ሲሉ ተያዙ የተባሉ እና በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎችን ለመጠቀም እንቅስቃሴ መጀመሩን ለማወቅ ተችሎአል።

የኢትዮጵያ ህዝብ በአቶ አንዳርጋቸው መያዝ ያሳየው ቁጣ ያስደነገጣቸው ደህንነቶች ለማንኛውም በሚል በደንበር አካባቢ ጥበቃቸውን እያጠናከሩ ነው። የአቶ አንዳርጋቸውን መያዝ ተከትሎ ግንቦት7ትን የሚቀላቀሉ ሰዎች መጨመራቸውንም ከድርጅቱ የወጣው መረጃ ያመለክታል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በቤልጂየም ብራሰልስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ኢህአዴግ አቶ አንዳርጋቸውን ለመያዝ የሄደበትን እርቀት ከማውገዝ በተጨማሪ የእንግሊዝ መንግስት የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ አጥብቆ እንዲከታተል ጠይቀዋል። ኢትዮጵያውያኑ ዛሬ በአውሮፓ ህብረት ቆንስላ ጽ/ቤት ፊት ለፊት የተቃውሞ ድምጻቸውን በከፍተኛ ቁጣ ከማሰማት በተጨማሪ፣ ያዘጋጁትን ደብዳቤ ለአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናትና ለእንግሊዝ መንግስት ኮንስላ ጽ/ቤት ሃላፊዎች አስረክበዋል።

Tuesday, 22 July 2014

ከአሁን በኋላ ብንወድቅም እየጣልን ነው የምንወድቀው!" ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ !!

በሰሜን ሸዋ የመርሃቤቴ ወረዳ ህዝብ ከወያኔ የፀጥታ ሃይሎችና ፌደራል ጋር ከባድ ውጊያ እያካሄደ ነው፣

ውጥረት በሰሜን ሸዋ መርሃቤቴ በርትቷል

ደብረብርሃን አከባቢ መግቢያና መውጪያ መንገዶች ተዘግተዋል።
ለወረዳው አለም ከተማና አካባቢዋ አገልግሎት ይውላል ተብሎ ከብዙ ጊዜ በሁአላ የገባውን መብራት የወያኔ መንግስት ህዝቡ የሚገለገልበትን መብራት አቁሞ ትራንስፎርሜሽኖቹን ነቅሎ ለአስቸኩአይ ጉዳይ ይፈለጋል ብሎ ወደ ትግራይ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የወረዳው 27ቱም ቀበሌ ተጠራርቶ ትራንፈርመሩን በቁጥጥር ስር በማድረግ ከላይ ከተጠቀሱት የወያኔ የፀጥታ ሃይሎች ጋር ኣሁን ድረስ ውጊኣ እያደረገ ሲሆን እስካሁን 7 የወያኔ ወታደሮች የሞቱ ሲሆን ከህዝብ ታጣቂ በኩል 1 ሞቷል። ባሁኑ ሰዓት ወረዳውን መሉ በሙሉ የህዝቡ ታጣቂ ተቆጣጥሮት ይገኛል። ወያኔ ከአዲስ አበባና ከተለያዩ አካባቢወች ተጨማሪ ሃይል ወደ አካባቢው እያንቀሳቀሰ መሆኑ ታውቁኣል።ሁኔታው የሚመለከታችሁ ወገኖች ሁሉ እየሆነ ያለውን ሁሉ በመከታተልና አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርጉ ያስፈልጋል።
ቁስለኞች ሆስፒታሉን አጣብውታል ። ቁስለኞቹ የሚታከሙት በፖሊስ ታጅበው ሲሆን ህክምናውን እንደጨረሱ ውእደ እስርቤት ይወሰዳሉ ።ከቦታው የሚደርሱ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስከመቼ ተታለን እንኖራለን የሚሉ የሰሜን ሸዋ ነዋሪዎች ዱር ቤቴ ብለው ሸፍተዋል። ከዚህ በታች የምትመለከቱት ከአከባቤው ከሚገኘው ሆስፒታል የተላከልንን ምስል ነው።
















Monday, 21 July 2014

የዞን 9 ጦማሪያን አባላት “ በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ” እጃችን ውስጥ ገባ!!

July 21, 2014
የዞን 9 ጦማሪያን አባላት “ በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ”  እጃችን ውስጥ ገባ!!
AbbayMedia:  ለጥረታቸው እያመሰገን ኢትዮጵያውያን በሙሉ ይህንን የኢንተርኔት ደኅንነት መጽሐፍ እውቀት እንዲጠቀሙበት እንመክራለን ።
ሙሉውን ዝርዝር እዚህ ላይ በመጫን ይመልከቱ፡-  https://securityinabox.org/am/howtobooklet
የኢንተርኔት ደኅንነት መጽሐፍ

 ይህ የኢንተርኔት ደኅንነት መጽሐፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ የኢንተርኔት ግንኙነት እንዲኖረን ማወቅ የሚያስፈልጉንን መሠረታዊ ነገሮች ለማብራራት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ነው። መመሪያው በኢንተርኔት ግንኙነት ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን በመለየትና በማብራራት፣ እነዚህን አደጋዎች ለመቀነስ የሚያስችል በተገቢ መረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንድንሰጥ ያስችለናል። ይህን ለማረጋገጥም ስምንት ከደኅንነት (ሴኵሪቲ)፣ ከመረጃ ጥበቃ (ዳታ ፕሮቴክሽን) እና ከጥብቅ ግንኙነት (ኮምዩኒኬሽን ፕራይቬሲ) ጋራ የተያያዙ ሰፋፊ ጥያቄዎችን ይመልሳል።

በእያንዳንዱ ምእራፍ መግቢያ የተነሳውን ርእሰ ጉዳይ ለማብራራት የተፈጠሩ ምናባዊ ክስተቶችና ገጸ ባህርያት ይገኛሉ። እነዚህ ገጸ ባህርያት የተወሰኑ ጉዳዮችን የሚያነሱበት እና የሚዘወተሩ ጥያቄዎችን የሚመልሱባቸው አጫጭር ምልልሶች በየምእራፉ ውስጥ ይገኛሉ። ከየምእራፉ የምንቀስማቸው ትምህርቶች ዝርዝርም በየምእራፉ ይቀርባል። በየምእራፎቹ የሚጋጣሙን በርካታ ቴክኒካዊ ቃላትና ስያሜዎች ትርጉም በመጽሐፉ መጨረሻ በማገናዘቢያ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በማብራሪያው ውስጥ የሚጠቀሱ ሶፍትዌሮችን በተመለከተ “በአጠቃቀም መመሪያ” (Hands-on Guides) ውስጥ ተጨማሪ ማጣቀሻዎች እናገኛለን። በዚህ “የመርጃዎች ስብስብ” (ቱልኪት) ውስጥ የሚገኝ ምእራፍ ወይም መመሪያ ተነጥሎ ለብቻው ሊነበብ ይችላል፤ በወረቀት ለማተምም (ፕሪንት) ሆነ በኤሌክትሮኒክ መልኩ ለሌሎች ለማካፈልም የተመቸ ነው። ሆኖም “የኢንተርኔት ደኅንነት በእጃችን” (Security in-a-box) መመሪያው የሚጠቅሳቸውን በመጽሐፉ እና በሶፍትዌር መመሪያው ውስጥ ተበታትንው የሚገኙትን ሊንኮች (links) እና ማገናዘቢያዎች በሚገባ ብንከተላቸው ከመመሪያው የበለጠ ተጠቃሚ እንሆናለን። የዚህ “እንጎቻ መጽሐፍ” (Booklet) የታተመ ቅጂ ካለን “የአጠቃቀም መመሪያውን” (Hands-on Guides) በምንጠቀምበት ጊዜ ሁሉ ከአጠገባችን ቢኖር መልካም ነው። በእንጎቻ መጽሐፉ ውስጥ ስለአንድ ዘዴ የተጻፈውን ምእራፍ ጨርሰን ሳናነብና ዘዴውን በሚገባ ሳንረዳው የዲጂታል ደኅንነታችን አስተማማኝ መጠበቂያ አድርገን ልንቆጥረው አይገባም።

የሚቻል ሲሆን የእንጎቻ መጽሐፉን ምእራፎች በቅደም ተከተል ማንበብ የተመረጠ ነው። የኢንተርኔት ደኅንነትን (ሴኵሪቲ) ማስጠበቅ ሒደት ነው። አንድ ተጠቃሚ ኮምፒውተሩ ከቫይረሶችና ከማልዌር (Malware) ነጻ መሆኑን ሳያረጋግጥ የኢንትርነት ግንኙነቶቹ ምሥጢራዊነት ፍጹም የተጠበቀ እንዲሆን ለማድረግ ቢፈልግ ሙከራው አስተማማኝ ውጤት ሊያመጣ አይችልም። ሌባው አስቀድሞ እቤት ውስጥ ከገባ በኋላ በሩን ከውጭ እንደሚቆልፍ ባለቤት መሆን ማለት ነው። ይህ ማለት በዚህ መጽሐፍ ከሚነሱት ርእሰ ጉዳዮች መካከል አንዱ ከሌላው የበለጠ አስፈላጊ ነው ማለት አይደለም። ነገር ግን ወደ በኋላ የሚመጡት ምእራፎች ተገልጋዮች አስቀድመው ያውቋቸዋል ብለው ታሳቢ የሚያደርጓቸው መረጃዎችና እውቀቶች ይኖራሉ፤ ለምሳሌ አዳዲስ ሶፍትዌሮች (software) የምንጭንበት ኮምፒውተራችን ስላለበት ሁኔታ አስቀድመን እንደምናውቅ ታሳቢ ይደረጋል።

በእርግጥ እነዚህን ምእራፎች ያለቅደም ተከተል ለማንበብ እና ለመጠቀም የሚያስገድዱ በቂ ምክንያቶች ሊያጋጥሙ ይችላሉ። በአጠቃቀም መመሪያው የተጠቀሱትን መሣሪያዎች/ሶፍትዌሮች መጫን ከመጀመራችን በፊት በኮሚፒውተራችን ውስጥ የሚገኙ እጅግ አስፈላጊ ፋይሎችን ወደ መጠባበቂያ ቋት መገልበጥን (back up) መማር ያስፈልገን ይሆናል። አለዚያም በምሥጢር መያዝ ያለባቸውን ፋይሎቻችንን በፍጥነት ለመደበቅ የሚያስገድድ ድንገተኛ ሁኔታ ሊገጥመን ይችላል፤ ይህ ደግሞ የሚገኘው በምእራፍ አራት ነው። ምናልባት ደግሞ ደኅንነቱ አስተማማኝ ባልሆነ የኢንተርኔት ካፌ ኮምፒውተር ስሱ መረጃዎችን ለመመልከት እንፈልግ ይሆናል። ለምሳሌ ያህል ከዚህ ኮምፒውተር በአገራችን የተከለከለ ድረ ገጽ ከፍተን መመልከት እንፈልጋለን እንበል፤ ይህን በቀላሉ ለመማር በቀጥታ “ማንነትን መደበቅ እና የኢንተርኔት ሳንሱርን ማለፍ” ወደሚለው ምእራፍ ስምንት እንዳንሔድ የሚከለክለን ነገር የለም።

1. ኮምፒውተርን ከማልዌር እና ከሰርጎ ገቦች (hackers) እንዴት መከላከል ይቻላል?
2. መረጃዎችን ከአካላዊ ጥፋት ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንችላለን?
3. አስተማማኝ የይለፍ (የምሥጢር) ቃል መፍጠር እና መጠቀም
4. በኮምፒውተራችን ውስጥ ያሉ ስሱ መረጃዎችን እንዴት መጠበቅ ይቻላል?
5. የጠፉ መረጃዎችን መልሶ ማግኘት የሚቻለው እንዴት ነው?
6. ስሱ መረጃዎችን በጥንቃቄ ማጥፋት የሚቻለው እንዴት ነው?
7. የኢንተርኔት ግንኙነታችንን በምሥጢር መያዝ ይቻላል? እንዴት
8. ማንነትን መደበቅ እና የኢንተርኔት ሳንሱርን/እገዳን ማለፍ
9. ደኅንነቱ የተጠበቀ የተንቀሳቃሽ (ሞባይል) ስልኮች አጠቃቀም
10. በማኅበራዊ ገጾች የራስን እና የመረጃዎችን ደኅንነት መጠበቅ
መፍቻ
ልብ ይበሉ የተከሰሱበትና “የወያኔ የመረጃ ስለላ ተቋም ማስረጃዪ ነው” ብሎ የያዘው ስለ ኢንተርኔት አጠቃቀም እውቀትን በማዳበራቸው ነው።ይህ ማንኛውም ተማሪ ወይም ሰው ሊያውቀውና ሊመራው የሚገባ የትምህርት አካል መሆኑንም የስለላ ተቋሙ ዘንግቶታል። ይሁን እንጂ ጦማሪዎቹ ለኢትዮጵያውያን የሚጠቅም ትምህርት በሚል ያዘጋጁቱን ትምህርት ሁሉም ሰው እንዲማርበት አጥብቀን እንመክራለን።

Sunday, 20 July 2014

Saturday, 19 July 2014 U.S. State Department deeply concerned about charges on Zone 9 Bloggers

                                        
Africa: Zone 9 Bloggers Charged by Ethiopian Court for Terrorism 07/18/2014 06:08 PM EDT Zone 9 Bloggers Charged by Ethiopian Court for Terrorism Press Statement Jen Psaki Department Spokesperson Washington, DC July 18, 2014 The United States is deeply concerned by the Ethiopian Federal High Court’s July 18 decision to press charges against six bloggers and three independent journalists under the Anti-Terrorism Proclamation. We urge the Ethiopian government to ensure that the trial is fair, transparent, and in compliance with Ethiopia’s constitutional guarantees and international human rights obligations. We also urge the Ethiopian government to ensure that the trial is open to public observation and free of political influence. We reiterate Secretary Kerry’s May 1 call on Ethiopia to refrain from using anti-terrorism laws as a mechanism to curb the free exchange of ideas. The use of the Anti-Terrorism Proclamation in previous cases against journalists, activists, and opposition political figures raises serious questions and concerns about the intent of the law, and about the sanctity of Ethiopians’ constitutionally guaranteed rights to freedom of the press and freedom of expression. Freedom of expression and freedom of the press are fundamental elections of a democratic society. The arrest of journalists and bloggers, and their prosecution under terrorism laws, has a chilling effect on the media and all Ethiopians’ right to freedom of expression. The Office of Website Management, Bureau of Public Affairs, manages this site as a portal for information from the U.S. State Department. External links to other Internet sites should not be construed as an endorsement of the views or privacy policies contained therein.

Friday, 18 July 2014

የፖለቲከኞቹ እስር እና ያስከተለው ሕገመንግሥታዊ ጥያቄ

                                          Wektawi62
ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ጋር ሰሞኑን ባደረጉት ቃለምልልስ የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከየመን ወደኢትዮጵያ ተላልፈው የመሰጠታቸው ጉዳይ በማንሳት “የኢትዮጵያ መንግስት የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሽፋንአድርጎ የሚመጣአሸባሪነትንአይታገስም”ማለታቸውን ዘግቧል።
     የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ በሀገር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት መካከል አቶ ሐብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከአንድነት፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ ፓርቲ፣ አቶ አብርሃ ደስታ ከአረና ትግራይ (ዘግይቶም ቢሆን ፍ/ቤት ቀርቧል)፣ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል። የጸረ ሽብር ግብረሃይል የግንቦት 7 ልሳን ከሆነው ኢሳት ቴሌቪዥን ጋር ግንኙነት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በቁጥጥር ስር ማድረጉን በደፈናው በዕለቱ የገለጸ ሲሆን የተያዙት የአንድነት፣ የሰማያዊና የአረና አመራሮች መሆናቸው ሲታይ መግለጫው እነሱን በቀጥታ የሚመለከት ስለመሆኑ የብዙዎች ግምት ሆኗል።
እስሩ እና የፓርቲዎች ምላሽ
     አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲዎች በተናጠል ሰሞኑን ባወጡት መግለጫ እስሩን ከመጪው ዓመት ምርጫ ጋር በቀጥታ አስተሳስረውታል። አንድነት በመግለጫው ኢህአዴግ የአንድነትን ከፍተኛ አመራሮች በማሰር የምርጫ ዘመቻውን ይፋ አድርጓል ብሏል። ሰማያዊ ፓርቲም በበኩሉ እስሩ ኢህአዴግ ቀጣዩን ምርጫ ያለተቀናቃኝ ለማለፍ የሚያደርገው ሕገወጥ እንቅስቃሴ አካል ነው ሲል ነቀፌታውን ሰንዝሯል።
   ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ ላይ በሕጋዊ መንገድ በፖለቲካ ፓርቲ በመደራጀት እናሽፋን በማድረግህገወጥ እንቅስቃሴን በማካሄድ መንግስትን በኃይል ለመለወጥ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ግለሰቦች አሁንም ከተጠያቂነት አያመልጡም ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ሕግ አስከባሪው፤ ሕግ ያለማክበር ጥያቄ ሲነሳበት፣
     የሕጎች ሁሉ የበላይ ሕግ የሆነው ኢትዮጵያ ህገመንግስት አንድ ሰው በሕግ ጥላ ስር ከዋለ በኋላ ቢበዛ በ48 ሰዓታት ፍርድቤት መቅረብ እንዳለበት ይደነግጋል። በተለይ የአንድነት እና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ፍ/ቤት ሳይቀርቡ ሰባት ቀናት ተቆጥረዋል። ይህም ብቻ አይደለም፤ በመረጡት ጠበቃ የመወከል መብታቸውንም ተጠቅመው ከጠበቆቻቸው ጋር የመገናኘት ዕድል መነፈጋቸውን ከፓርቲዎቹ የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ። አንድነት ይህን ድርጊት ሕገወጥ በማለት አካልን ነጻ የማውጣት ክስ በፍርድ ቤት መመስረቱን አስታውቋል። ይህም ሆኖ እስከትላንት(ማክሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2006) ማምሻውን ድረስ ተጠርጣሪዎቹ ፍ/ቤት ስለመቅረባቸው የታወቀ ነገር የለም።
አንድ የህግ ባለሙያ በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጡት አስተያየት “የሕግ የበላይነት በሚከበርበት ሀገር መንግሥት መረጃ አለኝ እስካለ ድረስ በሽብር ተግባር የተጠረጠሩ ሰዎችን ይዞ ማሰሩ አዲስ ነገር አይደለም። ነገር ግን ህግና ስርዓት እንዲከበር እተጋለሁ የሚል መንግሥት ራሱ ያወጣውን ሕገመንግስትን ጥሶ ያሰራቸውን ተጠርጣሪዎች በወቅቱ ወደፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ሲቀር የሕግ በላይነት የሚባለው ጉዳይ ያበቃለታል። በዚህ ምክንያት ዜጎች በመንግሥትና በሕግ ላይ ያላቸው አመኔታ የሚያጡ ሲሆን በቀጣይ ሕግና ስርዓትን አስከብራለሁ ብሎ የሚሞክራቸው ወይንም የሚናገራቸው ነገሮች ሁሉ በሕዝብ ዘንድ ተአማኒነትን ስለማይኖራቸው ትልቅ ችግር ይገጥመዋል” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።
በሰሞኑ ክስተት፤ የኢዴፓ አቋም
የኢትዮጽያዊያን ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) “በሽብርተኛነት ስም የሚወሰደው እርምጃ ግልጽነት ይኑረው” በሚል ርዕስ ከትላንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ የመንግሥት እርምጃ እንዳሳሰበው ጠቁሟል። መግለጫው እንዲህ እያለ ይቀጥላል «በሀገር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም መንግሥት በሽብር ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉ በሚዲዎች ተገልጿል። እነዚህ አመራሮች ከ48 ሰዓታት በላይ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውና የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መረጃ አለማቅረባቸው አመራሮቹ የታሰሩት በሚያራምዱት የፖለቲካ አቋም እንዳይሆን ፓርቲያችን ሥጋት አድሮበታል።
የኢዴፓ ስራ አስፈጻሚ ኮምቴ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተለውን አቋም ወስዷል።
  1. 1. መንግሥት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተያዙበትን ምክንያት ለህብረተሰቡ በዝርዝር እና ግልጽ መረጃ እንዲሰጥ፣
  2. 2. የታሰሩት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በሕገመንግስቱ አንቀጽ 21 መሠረት ለዜጎች የተሰጠው መብት እንዲከበርላቸው፣
  3. 3. በአስቸኳይ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ፣ የፍርድ ሒደታቸውም ተአማኒ፣ ግልጽ እና ፈጣን በሆነ መንገድ እንዲታይ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ግን አገሪቱ ሕግ አክብረን በሰላማዊ ትግል ከምንቀሳቀስ ፓርቲዎች ይልቅ በተቃራኒ የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች የሚያጠናክር፣ ክርክራቸውንም ምክንያታዊ የሚያደርግ እና የዴሞክራሲ ግንባታውን ወደኋላ የሚመልስ በመሆኑ ጉዳዩ በእጅጉ እንደሚያሳስበን እንገልጻለን። ስለዚህም መንግስት የጉዳዩን አሳሳቢነት ተገንዝቦ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ ኢዴፓ ያሳስባል።”
የፍረጃ ፖለቲካ
    የደርግ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በተደረገው የትጥቅ ትግል ወቅት ደርግ ታጋዮችን “ገንጣይ፣ አስገንጣይ፣ የእናት ጡት ነካሽ ወንበዴ….” እያለ የህዝብ ድጋፍ እንዳያገኙ ሌተቀን የመንግስት መገናኛ ብዙሃንን መሣሪያ በማድረግ ያወግዝ እንደነበረው ሁሉ አሁንም በተመሳሳይ ሁኔታ ኢህአዴግ ተቀናቃኞቹን በተደጋጋሚ በጠላትነት ሲፈርጅ፣ ሲያጥላላ ይታያል። በተቃዋሚ ፓርቲዎችም በኩል ተመሳሳይ ዝንባሌዎች የሚታዩ መሆኑ መቻቻልና በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንኳን አብሮ የመሥራት ባህል እንዳያድግ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።
    በዚህ ምክንያት ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ እና ብዙዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንኙነታቸው በጠላትነት መንፈስ ላይ የተመሰረተና መተማመን የሌለበት፣ ጥላቻ የነገሰበት ሆኖ እስከአሁን ዘልቋል። ኢህአዴግ በ2002 ምርጫ ከ99 በመቶ በላይ ወንበሮችን ካሸነፈ በኋላ ለንባብ የበቃው “አዲስ ራዕይ” መጽሔት በሐምሌ-ነሐሴ ወር 2002 ዓ.ም ዕትሙ ስለተቃዋሚዎች እንዲህ ይላል። “…አንዳንዶቹ ተቃዋሚዎች የተለመደውን የቀለም አብዮተኞች ስልት በመጠቀም የምርጫ ሕጎችን ሆን ብለው በመጣስ በሕጉ መሰረት እርምጃ ሲወሰድባቸው በነጻ መወዳደር አልቻልንም ብለው ኡኡ እንደሚሉ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነበር። እናም ስትራቴጂያችን እንደነዚህ ዓይነት ድርጊት ሲፈጸም መዋቅራችን የተሟላ መረጃ በቪዲዮ ጭምር እንዲይዝ፣ ይህንኑ መሠረት አድርጎ ድርጊቱን በሕዝብ ፊት እንዲያጋልጥና ሆን ተብሎ ምርጫውን ለማበላሸትና ብጥብጥ ለመፍጠር የተደረገ ተግባር መሆኑን እንዲያስረዳ፣ ሕጉ የተፈቀደለትን እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥቦ ነገሩን ለበላይ አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ነበር የሚያስቀምጠው። በዚሁ መሠረት የተቃዋሚዎች ሕገወጥ ድርጊት በየአካባቢው እንደነገሩ ሁኔታ በአገር አቀፍ ደረጃ በሰፊው የሚጋለጥበት ሁኔታ ተፈጠረ” ሲል የመተጋገሉን ደረጃ ያሳያል።
    እንዲህ ዓይነት አንዱ አጋላጭ ሌላው ተጋላጭ፣ አንዱ ሕግና ስርዓትን አክባሪ፣ ሌላው ጸረ ሕገመንግሥት፣ አንዱ ሽብርተኛ ሌላው የሠላም አቀንቃኝ አድርጎ የመሳሉ ጉዳይ ሞቅ በረድ እያለ አሁን ድረስ መቀጠሉ በሁለቱ ኃይሎች መካከል ያለው የፖለቲካ ልዩነት ወደአላስፈላጊ ጠርዝ የሚገፋ ሆኖ ይታያል።
    ከምንም በላይ ደግሞ መንግሥት በወንጀል ጠርጥሮ የያዛቸውን ሰዎች በወቅቱ ፍርድ ቤት ከማቅረብ መቆጠቡ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን አክብሮ የማስከበር ኃላፊነቱን አለመወጣቱን ያሳያል። ሕግና ሥርዓትን የማክበር ጉዳይ ደግሞ በምንም ዓይነት ምክንያት ሊስተባበል የማይችል መሆኑንም መንግሥት ይስተዋል ተብሎ ስለማይገመት ስህተቱን በፍጥነት ሊያርም ይገባል።
Now we all know “Truth”, "Love", "Reconciliation”, “Justice”, "Unity","Equality" and "Freedom" are not really people; but if they were, the ethnic apartheid regime of the TPLF would certainly arrest them and charge them as terrorists. These principles stand as the most dangerous of all opponents to a ethnic apartheid regime based on lies, division, ethnic hatred and oppression.
Perhaps this is why on April 25 and 26, the regime arrested Zone 9 bloggers or nine journalists-editor Asmamaw Hailegeorgis, freelancers Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, and bloggers Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu-and accused them of working with foreign human rights groups and using social media to create instability in the country
Yesterday they were charged with “terrorism” by the regime under their new and extremely vague anti-terrorism law that has been used as a tool to silence voices of freedom and has been widely criticized by human rights groups.
We will continue to use Truth, Love, Unity, Equality, Justice, Freedom and Principles of mercy, justice and right as our expert defense. If we are called a “terrorist” as a result of it, so be it. Almighty will give us courage and strength beyond ourselves if we ask.
Let us spread these “dangerous” principles of truth, reconciliation and justice so far, deep and wide that they become the pillars of a “New Ethiopia” where humanity comes before ethnicity and where we truly care about the freedom of our brothers and sisters like we care about our own! Let “justice roll on like a river, righteousness like a never-failing stream3!”

Thursday, 17 July 2014

ዜና - ሰበር ዜና:- ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ ክስ ተመሠረተ

                         ሰበር ዜና:-  ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ ክስ ተመሠረተ
በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት ጦማሪያን፣ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ አጥናፉ
ብርሃኔ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ እንዲሁም ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ ላይ ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የሽብርተኝነት ወንጀል በሚሰጠው ውጤት ሙሉ ተሳታፊ በመሆን ለአመፅ ተግባር በህቡዕ መደራጀታቸውን፣ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው የክስ ቻርጅ ይገልጻል፡፡

እንደ ዓቃቤ ሕግ ክስ ተጠርጣሪዎቹ በህቡዕ በመደራጀት፣ የአጭርና የቅርብ ጊዜ ግብ በማቀድና በመንደፍ ከግንቦት 2004 ዓ.ም. ጀምሮ እጃቸው እስከተያዘበት ጊዜ ድረስ በፓርላማ ሽብርተኛ ተብለው ከተሰየሙት የግንቦት 7 እና የኦነግ ድርጅቶች መመርያና ሐሳብ ሲቀበሉ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡

ከተጠርጣሪዎቹ አንዷ የሆነችው ሶሊያና ሽመልስ የቡድኑ መሥራችና አስተባባሪ በመሆን ከ2004 እስከ 2006 ዓ.ም. መቆየቷና ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ በውጭ አገር አስተባባሪና የውጭ ግንኙነት ሆና ከመሥራቷም በተጨማሪ፣ ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ተልዕኮ በመቀበል፣ አባላትን በማደራጀትና በመመልመል ስትሠራ መቆየቷን ክሱ ያስረዳል፡፡

የህቡዕ ቡድኑ ከ2004 እስከ 2006 ዓ.ም. ‹‹ሴኩሪቲ ኢን ቦክስ›› የተባለ ሥልጠና እንዲሠለጥንና እንዲደራጅ ስትመራ መቆየቷም በክሱ ተካቷል፡፡

ሌላኛው ተጠርጣሪ በፍቃዱ ኃይሉ የአገር ውስጥ የሽብር ቡድንን በመምራትና የሥራ ክፍፍል በማድረግ፣ እንዲሁም ግብ በማስቀመጥና ስትራቴጂ በመንደፍ ከሽብርተኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት ሲፈጥር መቆየቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡

የዓቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ከሆነ ተጠርጣሪ ናትናኤል ፈለቀ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ ካልተያዙ ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን የህቡዕ ድርጅቱ የአገር ውስጥ አስተባባሪ በመሆን በሥሩ ላሉት አባላት የሥራ ክፍፍል መመርያ በመስጠት፣ ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት በመፍጠር መመርያ ከመቀበሉ በተጨማሪ፣ ለአመፅ ተግባር የሚውል የተላከለትን 48,000 ብር ማከፋፈሉንም ክሱ ያብራራል፡፡

ሌሎቹ ተጠርጣሪዎች በህቡዕ ድርጅቱ ውስጥ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ መሥራችና አባል በመሆን የግንቦት 7 እና የኦነግን ስትራቴጂና ዕቅድ በመቀበል በውጭና በአገር ውስጥ ባሉ የቡድኑ አባላት ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በውጭና በአገር ውስጥ ሥልጠና በመውሰድ፣ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የሽብርተኝነት ድርጊት ለመፈጸም በማቀድ፣ በመዘጋጀት፣ በማሰርና በማነሳሳት ወንጀል መከሰሳቸውን ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ ያስረዳል፡፡

በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ሁለተኛ ክስ እንደሚያስረዳው ተጠርጣሪዎቹ በወንጀሉና በሚያስገኘው ውጤት ተስማምተው በሕገ መንግሥት ሥርዓት የተቋቋመን መንግሥት በአመፅ፣ በሁከትና በብጥብጥ ለመለወጥ በማሰብ ከግንቦት 2004 ዓ.ም. እስከተያዙበት ዕለት ድረስ በህቡዕ ተደራጅተው፣ የሥራ ክፍፍል በመፍጠር፣ ሥልጠናዎችን በመውሰድ፣ አመፅ የሚቀሰቅሱ ጽሑፎችን በመበተን፣ የአመፅ ቡድኖችን በማደራጀት ሕገ መንግሥቱና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በአመፅና በሁከት ለመለወጥ በመሞከር ወንጀል መከሰሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡    

Wednesday, 16 July 2014

Free Andargachew Tsige Rally-British Embassy Washington

16 JULY 2014 የመኢአድና የአንድነት የውህደት ጉዞ

                                         የመኢአድና የአንድነት የውህደት ጉዞ
ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም. ምርጫ 97ን ተከትሎ በወቅቱ ዋነኛ ተፎካካሪ በነበረው ቅንጅትና በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ መካከል የምርጫውን ውጤት መሠረት በማድረግ፣ በአዲስ አበባና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በመንግሥት ኃይልና ለተቃውሞ በወጡ ዜጐች መካከል በተፈጠረ ብጥብጥ ሳቢያ ከ200 በላይ ንፁኃን ዜጐች ሕይወት መቀጠፉ ይታወሳል፡፡

ለአጭር ጊዜ በተካሄደው ንቅናቄ የብዙኃን ኢትዮጵያውያንን ልብ መግዛት ችሎ የነበረው የአራት ፓርቲዎች ስብስብ የነበረው ቅንጅት፣ የምርጫው ውጤት ተጭበርብሯል በሚል ምክንያት ፓርላማ የመግባት ጥያቄውን መልሶ ለሕዝቡ አቀረበ፡፡ ይህን የፖለቲካ ውሳኔ ፓርቲው ራሱ መውሰድ ሲገባው ለምን መልሶ ወደ ሕዝብ አመጣው በሚል በበርካታ አካላት እስካሁንም ድረስ ይወቀሳል፡፡ 
መንግሥትም ምርጫው ተጭበርብሯል በተባለባቸው የተወሰኑ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ምርጫው እንዲደገም፣ ተጭበርብሯል የተባለው የምርጫ ውጤት ተቀባይነት እንዲያገኝና ተቃዋሚዎች ወደ ፓርላማ እንዲገቡ በርካታ ማሳሰቢያዎችና ማስጠንቀቂያዎች ሰጠ፡፡
ለወራት ከዘለቀው ከዚህ ሁሉ ንትርክና ጭቅጭቅ በኋላ ከምርጫው ውጤት ጋር በተያያዘ በአገሪቱ የተለያዩ ከተሞች በተለይ በአዲስ አበባ በጥቅምት ወር ዳግም ብጥብጥ ተቀሰቀሰ፡፡ ብጥብጡን ተከትሎ መንግሥት ጣቱን በወቅቱ የቅንጅት አመራሮች ላይ ሲቀስር፣ ተቃዋሚዎች ደግሞ መንግሥት አላስፈላጊና ያልተመጣጠነ ኃይል ተጠቅሟል በሚል መንግሥትን ወነጀሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አብዛኞቹ የቅንጅት አመራሮችና አንዳንድ አባላት ወደ ወህኒ ወረዱ፡፡ የቅንጅትም ህልውና ጥያቄ ምልክት ውስጥ ገባ፡፡ 
አብዛኞቹ የቅንጅት መሪዎችና አባላትም ከሁለት ዓመት በላይ ታሰሩ፡፡ ከእስር በይቅርታ ሲፈቱ ገሚሶቹ ወደ አውሮፓና አሜሪካ ሄደው የተለያየ የትግል ሥልት እንደሚከተሉ ሲያስታውቁ፣ የተቀሩት ደግሞ የተለያዩ ፓርቲዎችን በማቋቋምና በተለያዩ ፓርቲዎች ውስጥ በአባልነትና በአመራርነት የትግል ጉዞአቸውን ቀጠሉ፡፡ ይህም ክስተት በአገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ እንደ መልካምም እንደ መጥፎም ሒደት ተደርጐ የሚወሰድ ሆነ፡፡ ክስተቱን እንደ መልካም አጋጣሚ የሚመለከቱት ጉዳዩን በኢትዮጵያ የምርጫና የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሕዝቡ በያገባኛል ስሜት የተሳተፈበትና በምርጫ ካርድ መንግሥት መለወጥ እንደሚችል ማመኑን ሲሆን፣ መጥፎ ጐኑ ብለው የሚያነሱት ደግሞ የፓርቲው አመራሮች ከምርጫው በኋላ በወሰዱት ዕርምጃና አካሄድ በመከፋፈላቸው የተስፋውን ጭላንጭል ማጨለማቸውን በመጥቀስ ነው፡፡ 
የአንድነትና የመኢአድ ውህደት ሒደት
ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ የሚገኘው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ቅጥር ግቢ ውስጥ በርከት ያሉ ታዳሚዎች ድርጅቱ ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጋር ረዘም ላለ ጊዜ ሲያካሂደው የነበረው የውህደት ሒደት ፍሬ አፍርቶ ለቅድመ ውህደት ስምምነት መድረሱን ለመመልከት ተሰባስበዋል፡፡ የሁለቱ ፓርቲዎች ፕሬዚዳንቶች አቶ አበባው መሐሪና ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ሲጠበቅ የነበረውን የቅድመ ውህደት ስምምነት ተፈራርመው ይፋ አደረጉ፡፡ 
ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. የተካሄደው የሁለቱ ፓርቲዎች የቅድመ ውህደት ስምምነት በተለያዩ አጋጣሚዎች የታጀበ ነበር፡፡ የመኢአድ አባላት ነን የሚሉ ግለሰቦች በቅድሚያ የውስጥ ችግራችንን እንፍታ በሚል ጥያቄ ባስነሱት አምባጓሮ፣ በተወሰኑ ግለሰቦች ላይ የአካል ጉዳት ደርሶ እንደነበር በወቅቱ ተዘግቧል፡፡
ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. መንግሥት ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር በጋራ ሲሠሩ ደርሼባቸዋለሁ ያላቸውን አራት የፓርቲ አመራር አባላትን በቁጥጥር ሥር አዋለ፡፡ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የውህደት አመቻች ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው፡፡
የእርሳቸውን እስር ተከትሎ የሁለቱ ፓርቲዎች የውህደት አመቻች ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ፣ የውህደቱ ሒደት በምንም ዓይነት ሁኔታ እንደማይደናቀፍ በመግለጽ መንግሥት የወሰደው ዕርምጃ ሆን ተብሎ የሁለቱን ፓርቲዎች ውህደት የማደናቀፍ ሴራ ነው በማለት መንግሥትን ኮነነ፡፡ መንግሥት ለዚህ የሰጠው መልስ ደግሞ ዕርምጃው በምንም መንገድ ከምርጫም ሆነ ከሌላ ነገር ጋር የሚያገናኘው ነገር እንደሌለና ግለሰቦቹ የታሰሩት በሽብርተኝነት ወንጀል በመጠርጠራቸው ብቻ እንደሆነ አስረድቷል፡፡
ከእስር ዕርምጃውም በኋላ የሁለቱ ፓርቲዎች የውህደት ሒደት በተሳካና በታቀደለት መሠረት እየተጓዘ እንደሆነ የሁለቱም ፓርቲዎች ፕሬዚዳንቶች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ‹‹አሁን የውህደቱ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ነው፡፡ ብዙዎቹን ሥራዎች እያጠናቀቅን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ሐምሌ 19 እና 20 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠቅላላ ጉባዔው ተጠርቶ ውህደቱ ተፈጻሚ ይሆናል፤›› በማለት ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
የውህደት አመቻች ኮሚቴው ሐምሌ 3 ቀን 2006 ዓ.ም. አውጥቶት በነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ‹‹ሁለቱ ፓርቲዎች ውህደቱን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የውህደት አመቻች ኮሚቴ በማቋቋም ሥራቸውን በዕቅዳቸው መሠረት በትጋት እየሠሩ ሲሆን፣ የኮሚቴው ሰብሳቢ ወጣቱ ፖለቲከኛ አቶ ሀብታሙ አያሌው ነበር፡፡ ኮሚቴው እንደሚያምነው ሕወሓት/ኢሕአዴግ የሁለቱን ፓርቲዎች ውህደት ካለመፈለጉም በላይ፣ የተለያዩ ሁኔታዎችን በመጠቀም ለማደናቀፍ እንደሚሠራ እንገምታለን፤›› በማለት መንግሥትን ተጠያቂ አድርጓል፡፡ 
ምንም እንኳን የአመቻች ኮሚቴው መግለጫ ይህን ቢልም፣ የሁለቱም ፓርቲዎች ፕሬዚዳንቶች እንዳስረዱት የኮሚቴውን አባላት በማሰር ውህደቱ ላይ የሚያጠላው ምንም ዓይነት ነገር አይኖርም፡፡ 
ኢንጂነር ግዛቸው፣ ‹‹አንድ ፓርቲም ሆነ ማንኛውም ድርጅት ተቋማዊ አሠራር ይኖረዋል፤›› በማለት የአቶ ሀብታሙ አያሌው መታሰር ፓርቲው ተቋማዊ አሠራር የሚከተል በመሆኑ ያን ያህል ችግር እንደማይፈጥር ገልጸዋል፡፡ 
ኢንጂነሩ ሲቀጥሉም፣ ‹‹የአመራሮች ለተወሰነ ጊዜ በቦታቸው አለመኖር የራሱ የሆነ ተፅዕኖ ቢኖረውም ያንን ሁኔታ ግን በተቋማዊ አሠራር እናስተካክለዋለን፤›› በማለት የአባላት መታሰር የራሱ የሆነ ተፅዕኖ እንዳለው ሆኖ ሥራዎች በታቀደለት መሠረት እየተካሄዱ እንደሆነ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡
የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ በበኩላቸው፣ ‹‹የልጁ መታሰር ቢያሳስበንም በውህደቱ ላይ የሚያስከትለው አንዳችም ነገር አይኖረውም፤›› በማለት ለሪፖርተር ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡
ከሁለቱም ፓርቲዎች የተውጣጡ አሥር አባላት ያሉት የውህደት አመቻች ኮሚቴ የውህደቱን ሒደት የተመለከቱ የፋይናንስ፣ የሰነድ ዝግጅት፣ የሕዝብ ግንኙነትና የሎጂስቲክስ ሥራዎችን እንደሚሠራ የገለጹት ኢንጂነር ግዛቸው፣ ‹‹የሰነድ ዝግጅት ኮሚቴው አብዛኛውን ሥራውን አጠናቋል፤›› ያሉ ሲሆን፣ ይህ ኮሚቴም የውህዱ ፓርቲን ፕሮግራምና ደንብ አዘጋጅቶ እንዳጠናቀቀ፣ ሐምሌ 19 እና 20 የሚካሄደውን የውህደት ሥራ ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቁንም አብራርተዋል፡፡ 
ፋይናንስን በተመለከተም፣ ‹‹የሚያስፈልገውን በጀት አውጥተን ያንን በጀት የምንሸፍንበትን መንገድና የገንዘብ ምንጭ እያፈላለግን ነው፤›› በማለት የውህደቱን ሒደት አስረድተዋል፡፡ 
ሐምሌ 19 እና 20 ቀን 2006 ዓ.ም. ለሚካሄደው የውህደት ሥነ ሥርዓት በመላው አገሪቱ ከሚገኙ የሁለቱ ፓርቲዎች አባላት መካከል 800 የሚሆኑ አባላት እንደሚገኙ የገለጹት የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው፣ እነዚህ በርከት ያሉ አባላትን ወደ አዲስ አበባ ለማምጣት የሎጂስቲክስ ሥራ እየተሠራ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ 
በ1997 ዓ.ም. ተነሳስቶ የነበረውን የሕዝብ መንፈስ እንመልሳለን በማለት እየሠሩ እንደሆነ የሚገልጹት ሁለቱ ፓርቲዎች፣ በወቅቱ ተፈጥሮ የነበረው ዓይነት ስህተት እንዳይደገም ካለፈው ትምህርት መውሰዳቸውን በመጥቀስ፣ የሕዝቡን ተነሳሽነት እንደ አዲስ ለመመለስ እየሠሩ እንደሆነ በሚያወጧቸው መግለጫዎች አስረድተዋል፡፡ 
ሁለቱ ፓርቲዎችና ሌሎች ፓርቲዎች
የሁለቱ ፓርቲዎች ውህደት አመቻች ኮሚቴ ሌሎች ፓርቲዎችም ወደ ትብብር በመምጣት የአገሪቱን የፖለቲካ ሁኔታ ለመቃኘት በጋራ እንሥራ የሚል ጥሪ ለተለያዩ ፓርቲዎች ማስተላለፉን የሁለቱ ፓርቲዎች ፕሬዚዳንቶች አስታውሰዋል፡፡ ይሁን እንጂ በተለይ መድረክ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ የሁለቱን ፓርቲዎች ውህደት የሌሎች ፓርቲዎችን ግንኙነት በማይጐዳ ሁኔታ መካሄድ አለበት በማለት፣ የሁለቱ ፓርቲዎች የውህደት ሒደት ሁሉን አቀፍ እንዲሆን ከመጠየቁም በተጨማሪ፣ አንድነት እንደ መድረክ አባልነቱ የፓርቲውን ሕግና ደንብ አክብሮ እንዲሠራ አሳስቧል፡፡ 
የፓርቲውን ሕግና ደንብ አክብሮ የማይሠራ ከሆነ ከዚህ ቀደም ከወሰደው የቃላት ማስጠንቀቂያ የዘለለ ውሳኔ እንደሚወስድም አስታውቆ ነበር፡፡ ነገር ግን የአንድነት ፕሬዚዳንት ለዚህ ጉዳይ ሲመልሱ፣ ‹‹ጉዳዩን የሚዲያ ምልልስ ማድረግ አንፈልግም፤›› ብለው ነገር ግን፣ ‹‹ይህንን ሁኔታ የምናየው አጠቃላይ የፓርቲዎች ትብብር አድርገን ነው፤›› በማለት የአንድነትና የመኢአድ ውህደት ማንንም ለመጉዳት ያላለመና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተጠናከረ ሁኔታ በጋራ እንዲሠሩ ካለው ፅኑ ፍላጐት የመነጨ እንደሆነ ለሪፖርተር አብራርተዋል፡፡ 
‹‹እኛ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በቅድሚያ ውህደት እንዲፈጥሩ አስፈላጊውን እንቅስቃሴ እያካሄድን ነው፡፡ ውህደት ተፈጥሮ ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ አዲስ ፓርቲ መፈጠር አለበት የሚል እምነት በመያዛችን በእርሱ ላይ እየሠራን ነው፤›› ያሉት የአንድነት ፕሬዚዳንት፣ ‹‹ውህደት የማይፈልጉ ፓርቲዎች ደግሞ ካሉ ከውህደቱ ባለፈ ሁኔታ በትብብር፣ በፕሮግራምና በፕሮጀክት አብረን ለመሥራት ሁልጊዜም ዝግጁ ነን፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ይህን ቢሉም ግን ቀጣዩ የመድረክና የአንድነት ግንኙነት የሚወሰነው አዲስ በሚፈጠረው ውህዱ ፖለቲካ ፓርቲ አማካይነት እንደሆነም ጠቅሰዋል፡፡ ‹‹ውህዱ ከተፈጸመ በኋላ የመኢአድም ሆነ የአንድነት ሕጋዊ ህልውናቸው ያከትማል፡፡ ያን ጊዜ አንድነት ስለሌለ በመድረክ በኩል ምንም የሚደረግ ነገር አይኖርም፤›› በማለት፣ በሁለቱ ፓርቲዎች መፃኢ ግንኙነት ላይ ወሳኝ የሚሆነው ውህዱ ፓርቲ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
አቶ አበባው መሐሪ በበኩላቸው መዋሀድ ለሁሉም የሚጠቅም እንደሆነ ገልጸው፣ ‹‹መዋሀድ ይጐዳል ማለት ሞኝነት ይመስለኛል፤›› በማለት የመዋሀድን ጠቀሜታ ሲያስረዱ፣ እንደ ኢንጂነር ግዛቸው ሁሉ ሁለቱም ፓርቲዎች ውህደት የሚያካሂዱት በጋራ ለመሥራትና የተጠናከረ አንድ ኃይል ለመፍጠር እንጂ፣ የትኛውንም ተቃዋሚ ፓርቲን ለመጉዳት ባለመ መንገድ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሁኔታ በቅርብ የሚከታተሉ ምሁራንና አስተያየት ሰጪዎች አብዛኞቹ ፓርቲዎች ውህደት፣ ቅንጅትም ሆነ ጥምረት ለመመሥረት ሲሠሩ የሚታዩት ምርጫ ሲቃረብ ነው በማለት የሚተቹ ሲሆን፣ የመኢአድና የአንድነት ፓርቲ ፕሬዚዳንቶች ግን ይህ ዓይነት አስተያየት እነሱን እንደማይወክል ይናገራሉ፡፡ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ሁለቱ ፓርቲዎች የውህደት ድርድር የጀመሩት በመጪው ዓመት የሚካሄደውን ምርጫ ታሳቢ በማድረግ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሳይሆን፣ ቀደም ብሎ ከአራት ዓመታት በፊት የተጀመረ እንደሆነ ያብራራሉ፡፡
በአገሪቱ ውስጥ በርከት ያሉ በጋራ የመሥራት ስምምነቶች በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ቢደረጉም፣ አብዛኞቹ የተነሱለትን ዓላማ ከግብ ሳያደርሱ ወደ መክሰም እንደሚያመሩ በመጥቀስ የሚተቹ ደግሞ፣ ብዙዎቹ ፓርቲዎች በጋራ የመሥራት ስምምነት የሚፈጽሙት ምርጫ ሲደርስ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡ ከአራት ዓመት በፊት የተጀመረው የአንድነትና የመኢአድ የውህደት ሒደትም በአገሪቱ የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ የሚያስከትለውን ለውጥና የተለየ ውጤት የማምጣት ዕድል ወደፊት የሚገመገም እንደሆነም እነዚሁ ተቺዎች ይከራከራሉ፡፡        

በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ ዓመፅ ተጀመረ…!!!

JULY 16, 2014

የሃረማያ ዩኒቨርሲት የድህረ ምረቃ ተማሪዎች የመመረቅያ ፅሑፍ ክፍያ ከዕጥፍ በላይ በመጨመሩ ዓመፅ ኣስነስተዋል።
ተማሪዎቹ ከትናንት በስትያ ሰኞ ሓምሌ 7 /2006 ዓ/ ም ክፍያው 3000ብር እንደሆነ ከዩኒቨርስቲው ሬጅስትራር የተፃፈ ደብዳቤ የተሰጣቸው ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው ሃሳቡ በመቀየር ክፍያው ወደ 8700 ብር ከፍ በማድረግ በቦርድ ለጥፎዋል።
ተማሪዎቹ ተሰባስበው ወደ ዩኒቨርሲቲው ሃላፊዎች የሄዱ ሲሆኑ ክፍያው ከዕጥፍ በላይ እንዲሆን የተደረገበት ወሳኔ ኣግባብነት እንደሌለውና ወደ ቀድመው መጠን ካልተስተካከለ እንደማይመዘገቡ ኣሳውቀዋል።
እንደምጫችን ኣገላለፅ ከሆነ ክፍያው ባንዴ ከእጥፍ በላይ እንዲሆን የትደረገው የመንግስት ሰራተኞች ደምወዝ ጭማሪ ተደርገዋል የሚል እንደሆነ ኣረጋግጠዋ።
የሁኒቨርስቲ ኣስተዳደር በጉዳዩ ኣስቸኳይ ስብሰባ እያካሄደ እንደሆነም ለማወቅ ተችለዋል።
ሃረማያ ዩኒቨርስቲ ልማታዊ መንግስታችን ስግብግብ ዩኒቨርሲት ብሎ ታፔላ እንደሚለጥፍለት ይጠበቃል።
“ስግብግብ ነጋደዎች” ነው…! ያለው በኢቲቪ እየተናገረ የሰማሁት ኣንዱ ቱባ ባለስልጣን።
ዓመፁ በኣግባቡ ይፈታ ይሆን? ወይስ እንደ ተለመደው መቺ ሃይል ይላካል…?

Tuesday, 15 July 2014

ፍርድ ቤቱ በእነ ሐብታሙ ጉዳይ ትዕዛዝ አስተላለፈ

July 15th, 2014
                 10557351_10202411521670248_5400861717310665444_n
የዛሬ ሳምንት ማክሰኞ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረጉት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ህገ መንግስቱና የጸረ ሸብር አዋጁ በሚያዙት መሰረት እጃቸው ከተያዘበት አንስቶ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እንደሚገባቸውና በቤተሰቦቻችውና በጠበቃቸው መጉብኘት መብታቸው መሆኑን ከግምት በማስገባት ጠበቆቻቸው ያልተሟሉላቸው መብቶች በፍርድ ቤት ጣልቃ ገብነት ይከበሩ ዘንድ በዛሬው ዕለት ክስ መስርተው የማዕከላዊ አመራሮች ለቀረበባቸው ክስ በአካል በመገኘት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ሃላፊዎቹ ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ምላሽ ሰዎቹን ፍርድ ቤት በ2/11/2006 ዓ.ም ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል፡፡የታሳሪዎቹ ጠበቆች የሆኑት ጠበቃ ተማም አባቡልጉና አቶ ገበየሁ ደምበኞቻቸውን ማግኘት አለመቻላቸውን ፍርድ ቤት ሲቀርቡም እንዲያውቁ አለመደረጋቸውን አስረድተዋል፡፡ጠበቆቹ ደምበኞቻቸውን ማየት እንዲፈቀድላቸውና በቤተሰቦቻቸውም እንዲጎበኙ እንዲደረግ ትዕዛዝ እንዲሰጥ አቤት ብለዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ ታሳሪዎቹ በቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኙ እንዲደረግና ከጠበቆቻቸው እንዲመካከሩ ይደረግ ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ፍርድ ቤቱ ከዚሀ በተጨማሪም በማዕከላዊ እንደሚገኙ የተነገረላቸውን ታሳሪዎች የፊታችን አረብ 4፡00 እንዲቀርቡ ሲል አዟል፡፡የማዕከላዊ ኃላፊም በፍር ቤቱ የተሰጠውን ትዕዛዝ መፈጸሙን እንደሚከታተሉ ተናግረዋል፡፡

የግለሰብ ነፃነት ሲገፈፍና መብቱ ሲረገጥ በዝምታ ማለፍ ውጤቱ ሽንፈት ይሆናል፦


  • 92
     
    Share
ዘረኛው የወያኔ ቡድን የሥልጣን ርካቡን በጠመንጃ ኃይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ስለደረሰው ግፍ፤ሥቃይና መከራ እንዲሁም አገሪቱን በቋንቋና በጐሣ ሸንሽኖ ህልውናዋን እየተፈታተነ ለመሆኑ በልዩ ልዩ አጋጣሚዎች በተደጋጋሚ ተገልጿል።
የዚህን ጠባብ ብሄረተኛ ቡድን እኩይ ተግባር በቡድንም ሆነ በተናጠል በብዕራቸው የተዋጉ፤በድርጅት ዙሪያም ተሰባስበው ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ትግል ያካሄዱ ኢትዮጵያውያን በነቂስ እየተለቀሙ ለእሥር ተዳርገዋል።ከፊሉንም ቤት ይቁጠረውና የደረሱበት ሳይታወቅ እንደወጡ ቀርተዋል።
ሰሞኑንም ይህ መንግሥት ነኝ ባይ ጠባብ ብሄረተኛ ቡድን ከየመን መንግሥት ጋር በመመሳጠር ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብትን ድንጋጌ ጥሶ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የግንቦት ሰባት የፍትህ፤የነጻነትና የዴሞክራሲያው ንቅናቄ መስራች አባልና የንቅናቄውን ዋና ጸሐፊ በማገት ጠልፎ እንደ አንድ ነጻ ዜጋ በየትኛውም አገር የመዘዋወር መብታቸውን ረግጦ በማፈን ወደ ኢትዮጵያ ውስዶ እያሰቃያቸው ይገኛል።
መብቴ ተረገጠ፤ ነፃነቴ ተደፈረ፤በሀገሬ ጉዳይ የመናገር፤የመጻፍና የመደራጀት ዜግነታዊ ሕልውናየ ተጣሰ…ወዘተ ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከምን ጊዜውም በላይ ይህ የሰሞኑ በወንድማችን ላይ የተፈፀመው ድርጊት አስቸኳይ መልስ የሚጠይቅ ፈተና ከፊቱ ተደቅኖ ይገኛ
ል።ይህን ፈተና ለመጋፈጥ የማይሻ ሁሉ የዘረኛውና የጠባብ ብሄረተኛው የወያኔ መንግሥት ጋሻ ጃግሬ ወይንም ከዚህ ወንበዴ ቡድን ተጠቃሚ የሆነ ብቻ ነው።
በሁለተኛው የዓለም ጦርነት መባቻ ላይ የሂትለርን አገዛዝ አጥብቆ የሚያወግዝ ማርቲን ኒሞለር የተባለ ጀርመናዊ የፕሮቴስታንት ቄስ በወቅቱ ሰፍኖ የነበረውንና ናዚስቶች ደረጃ በደረጃ ይፈጽሙ የነበረውን ግፍና መከራ አስመልክቶ የተናገረውን ያስታውሷል፦ይኸውም
“የናዚ አገዛዝ በመጀመሪያ በሶሻሊስቶች ላይ ሲዘምት ምንም አልተናገርኩ ምክንያቱም እኔ ሶሻሊስት ስለአልነበርኩ ።ቀጥለውም በትሬድ ዩኒየን ላይ የግፍ በትራቸውን ሲሰነዝሩ አልተናገርኩም።ምክንያቱም እኔ ትሬድ ዩኒየኒስት አልነበርኩምና። ከዚያም በኋላ በይሁዶች ሲነሱ ዝም አልኩ ምክንያቱም እኔ ይሁዲ አልነበርኩምና።በመጨረሻም ወደ እኔ መጡ ሆኖም ግን ስለ እኔ የሚናገር የቀረ ማንም አልነበረም።”
አሁንም ይህ በአንድ ታጋይ ኢትዮጵያዊ ላይ የተፈጸመውን ዘግናኝ ድርጊት መግለጫ በማውጣት ፤ሰልፍ በመሰለፍ ብቻ ልንወጣው አይቻለንም።በመሆኑም እኛ በኮሎምቦስ ኦሀዮ የምንገኝ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰው በደል በዝምታና በለሆሳስ ልናስተናግደው በጭራሽ አይቻለንም።ይህ ዓይነት መረን የለቀቀ ግፍ ተራ በተራ በእያንዳንዱ የተቃዋሚ ድርጅት መሪዎችና የዴሞክራሲ ጠበቃዎች ላይ ከመድረሱ በፊት በድርጅት መጠናከርንና በመረጃ ልውውጥ ውጤታማ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ እንደሆነ የወቅቱ አጠቃላይ ሁኔታ ስለሚያሳይ ለእውነተኛ የኢትዮጵያ ልጆች የሚከተለውን ጥሪ አቅርበናል።
vየየመን መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ የፈጸመችው አሳልፎ የመስጠት ክህደትን ማጋለጥ። የእንግሊዝ መንግሥት የዜጋዋን መብት ለመታደግ በመጀመሪያው ረድፍ መገኘት ስላለባት የሚፈለገውን ሁሉ ስልት በመጠቀም ለጉዳዩ ትኩረት እንድትሰጥበትጫና ማድረግ።

vበውጭ አገር የሚገኘው ኢትዮጵያዊ በያለበትና በሚገኝበት ሥፍራ የተገኘውን አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅሞ ለተወካዮች ምክር ቤትና ለሴነተሮች ለማሳወቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ።አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእንግሊዝ ዜጋ መሆናቸው እየታወቀ የየመን መንግሥት ዓለም አቀፉን የሰብዓዊ መብት ሕግጋትን ፤ የኮመን ዌልዝ ኔሽንን ፓክት ጥሶ ለዘረኛው መንግሥት አስልፎ የሰጠበትን ምክንያት አጥጋቢ ምላሽ ከሁለቱም መንግሥታት እንዲሰጥ አበክረን እንጠይቃለን።

vየወያኔ የዜና አውታሮች የሚያሰራጩትን ነጭ ወሬ የሚያስተጋቡ ግለሰቦች እንዳሉ ይታወቃል። እነዚህ ግለሰቦች  በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚያሰራጩት ወሬ እርባና ቢስ ቢሆንም የአንድነት ኃይሉን የሚጎዳ በመሆኑ ከዚህ ጸረ-ሕዝብ ተግባራቸው መቆጠብ ይኖርባቸዋል። በሌላም በኩል በየአካባቢያችን የሚገኙ የዘረኛው መንግሥት ሰላዮች፤ደጋፊዎችም ሆነ ተባባሪዎች የቆሙበት ዓላማ ርካሽ ሀገርንና ወገንን የሚጎዳ በመሆኑ በመረጃ ላይ  የተደገፈ ተግባራቸውን በማረጋገጥ ከማህበራዊ ግንኙነት ማግለል በእነርሱ በኩል የሚከናወኑ ማናቸውንም ነገሮች ቦይ ኮት ማድረግ።


vየአንድነት ኃይሎ ተበታትኖ መገኘቱ ለጥቃት በር እንደከፈተ ይታመናል በመሆኑም ሁኔታው ትግላችንንም እየጎዳው የጠባብ ብሄረተኛውን የወያኔን እድሜም እያራዘመው በመገኘቱ የአንድነት ኃይል ነን ብለው የሚያምኑ የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ ንቅናቄዎች በአስቸኳይ በመገናኘት የኢትዮጵያ አንድነት የተቃዋሚ ኃይልን መመስረት ይገባቸዋል።የዚህ የኢትዮጵያ አንድነት ኃይል መመሥረት ለመንግሥታትም እንደ አማራጭ ኃይል ሆኖ ስለሚቀርብ ይህንኑ ዓላማ ገቢራዊ ለማድረግ የየድርጅቶችም ሆነ የየስብስቦቹ መሪዎች ከዚህ በፊት በባዶ ጉዳይ የሚያናቁራቸውን ሁሉንም ነገር ከበስተጀርባቸው በመተው ለአዲስ ትንሳኤና የድል ጉዞ እንዲነሱ ታፍራና ተከብራ በኖረችውና በእኛ ዘመን ለውርደት በተዳረገችው ታላቋ ሀገራችን በኢትዮጵያ ስም እንጠይቃለን።

vበወንድማችን ላይ የተፈፀመውን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በጥሞና ተመልክተን መደረግ ስለሚገባው ልዩ ልዩ የትግል እንቅስቃሴ ስልቶችን የሚነድፍ፤ የሚያጠናና በተግባር የሚተረጉምና የሚመራ ውጤታቸውንም የሚገመግም፤ ራሱን የቻለ በስደት ላይ የሚገኘውን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያሳትፍ አንድ ለስደተኛው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ማዕከል መፍጠር እንደሚገባው እናምናለን።የዚህ ማዕከል መፈጠር በተለያየ መልክ ጸረ-ሕዝብ የሆነው ህወሃት በተቃዋሚ ኃይሎች ላይ የሚያደርሰውን በደል፤ ሰቆቃና መከራ በባለቤትነት ወስዶ መምራት ይሆናል።ይህንን ሀሳብ ግምት ውስጥ በማስገባት ዳብሮ አንድ ውጤት ላይ እንዲደርስ አበክረን እንጠይቃለን።

ኢትዮጵያ ለዘላዓለም ትኑር!!

ESAT DC Daily News 14 July 2014

Monday, 14 July 2014

ሰበር ዜና










                                 


                         ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት (ሁማን ራይት) ዛሬ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ባሰራጨው ዜና  የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከእንግሊዝ ለኢትዮጵያ  ዕርዳታ የሚሰጡ ድርጅቶች በሙሉ (የእንግሊዝ መንግሥትንም ጨምሮ) ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ  መብት ይዞታ ቅድምያ መስጠታቸውን እና አለመስጠታቸውን በሚያጣራ መልኩ ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግ ያሳለፈውን ውሳኔ  ''ጠቃሚ እርምጃ'' በማለት አሞካሽቶታል።
ውሳኔው በተለይ በቅርቡ ከአርበኛ አንዳርጋቸው ፅጌ መታገት በኃላ የእንግሊዝ መንግስት  ''የባህር ማዶ የልማት ትብብር ድርጅት'' (UK Department for International Development (DFID) ) ለኢትዮጵያ መንግስት የገንዘብ ድጎማ ሊያደርግ የነበረ ከመሆኑ አንፃር የዛሬው ውሳኔ ከፍተኛ መልዕክት ማስተላለፉ አይቀርም።በሌላ በኩል የዛሬው የፍርድቤቱ ውሳኔ ይሄው የልማት ድርጅት (DFID) በበቂ ሁኔታ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ ይዞታ ጉዳይ አለመመርመሩን ጠቁሞ በእዚሁ አዲሱ የፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግበት ማዘዙን ያብራራል።
የዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የእርምጃውን ፋይዳ ሲያስረዳ  የድርጅቱ የአፍሪካ ክፍል ተጠሪ የተናገሩትን በመጥቀስ ነው።እንዲህ ይነበባል -

''የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድቤት ውሳኔ ለሌሎች መንግሥታት እና እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የማንቅያ ጥሪ ነው።ምክንያቱም ሀገራትም ሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የሚሰጡትን የልማት ፕሮግራም ሁሉ ቅድምያ ከሰብዓዊ ይዞታ አንፃር እንዲመለከቱ ያደርጋል''ይላል።

የዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት (ሁማን ራይት) ስለ እንግሊዙ ከፍተኛ ፍርድቤት የዛሬ ውሳኔ አስመልክቶ ያወጣውን ዘገባ ከእዚህ በታች ይመልከቱ።

Ethiopia: UK Aid Should Respect Rights
Ruling Permits Review of Development Agency’s Compliance
JULY 14, 2014

(London) – A UK High Court ruling allowing judicial review of the UK aid agency’s compliance with its own human rights policies in Ethiopia is an important step toward greater accountability in development assistance.

In its decision of July 14, 2014, the High Court ruled that allegations that the UK Department for International Development (DFID) did not adequately assess evidence of human rights violations in Ethiopia deserve a full judicial review.

“The UK high court ruling is just a first step, but it should be a wake-up call for the government and other donors that they need rigorous monitoring to make sure their development programs are upholding their commitments to human rights,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “UK development aid to Ethiopia can help reduce poverty, but serious rights abuses should never be ignored.”

The case involves Mr. O (not his real name), a farmer from Gambella in western Ethiopia, who alleges that DFID violated its own human rights policy by failing to properly investigate and respond to human rights violations linked to an Ethiopian government resettlement program known as “villagization.” Mr. O is now a refugee in a neighboring country.

Human Rights Watch has documented serious human rights violations in connection with the first year of the villagization program in Gambella in 2011 and in other regions of Ethiopia in recent years.

A January 2012 Human Rights Watch report based on more than 100 interviews with Gambella residents, including site visits to 16 villages, concluded that villagization had been marked by forced displacement, arbitrary detentions, mistreatment, and inadequate consultation, and that villagers had not been compensated for their losses in the relocation process.

People resettled in new villages often found the land infertile and frequently had to clear the land and build their own huts under military supervision. Services they had been promised, such as schools, clinics, and water pumps, were not in place when they arrived. In many cases villagers had to abandon their crops, and pledges of food aid in the new villages never materialized.

The UK, along with the World Bank and other donors, fund a nationwide development program in Ethiopia called the Promotion of Basic Services program (PBS). The program started after the UK and other donors cut direct budget support to Ethiopia after the country’s controversial 2005 elections.

The PBS program is intended to improve access to education, health care, and other services by providing block grants to regional governments. Donors do not directly fund the villagization program, but through PBS, donors pay a portion of the salaries of government officials who are carrying out the villagization policy.

The UK development agency’s monitoring systems and its response to these serious allegations of abuse have been inadequate and complacent, Human Rights Watch said. While the agency and other donors to the Promotion of Basic Services program have visited Gambella and conducted assessments, villagers told Human Rights Watch that government officials sometimes visited communities in Gambella in advance of donor visits to warn them not to voice complaints over villagization, or threatened them after the visits. The result has been that local people were reluctant to speak out for fear of reprisals.

The UK development agency has apparently made little or no effort to interview villagers from Gambella who have fled the abuses and are now refugees in neighboring countries, where they can speak about their experiences in a more secure environment. The Ethiopian government’s increasing repression of independent media and human rights reporting, and denials of any serious human rights violations, have had a profoundly chilling effect on freedom of speech among rural villagers.

“The UK is providing more than £300 million a year in aid to Ethiopia while the country’s human rights record is steadily deteriorating,” Lefkow said. “If DFID is serious about supporting rights-respecting development, it needs to overhaul its monitoring processes and use its influence and the UK’s to press for an end to serious rights abuses in the villagization program – and elsewhere.”