Thursday, 28 August 2014

ሰበር ዜና የኢትዮዽያ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሲውዲን አለማቀፍ ፍርድ ቤት ክስ ተመሰረተባቸው።

አስራሦስት የኢትዮዽያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የጦር መኮንኖች በሲዊዲን አለም አቀፍ የጦር ፍርድቤት ተከሰሱ።
እነሱም
1-አርከበእቁባይ
2-በረከት ስምሆን
3-አባዱኣ ገመዳ
4-ሳሞራ የኑስ
5-አባይ ፀአዬ
6-አሰፋ
7-ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ
8-አሰን ሺፋ
9-ሙሉጌታ በርሄ
10-ነጋ በርሄ
11-ወርቅነህ ገበየው
12-ኮማንደር ሰመረና አንድ ስማቸው ያልተገለጠ ሰው በግድያ፡ አስገድዶ መድፈር በስቃይ፡ ሰዎችን በማንገላታት፡ በህገወጥ ሁኔታ በማሰር ፡በሙስና ክስ ቀርቦባቸዋል።

Tuesday, 26 August 2014

በአምስት ሣምንታዊ መጽሔቶችና አንድ ጋዜጣ ላይ የተመሰረተውን ክስ ተከትሎ አስራ አንድ ጋዜጠኞች ለስደት ተዳረጉ። አስራ አንዱ ጋዜጠኞች የተሰደዱት በፍትህ ሚኒስቴር ሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. “የዐመጸ ቅስቀሳና የሐሰት ወሬዎችን በመንዛት ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ ጥረት አድርገዋል” በሚል በተመሰረተባቸው ክስ መሆኑን ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ የደረሰን መረጃ ያስረዳል።
140823-11-journalists-fledፍትህ ሚኒስቴር ክስ የመሰረተባቸው ሎሚ፣ ዕንቁ፣ ፋክት፣ ጃኖ እና አዲስ ጉዳይ መጽሔቶች እና አፍሮ ታይምስ ጋዜጦች ሲሆኑ፤ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ አስራ አንድ ጋዜጦች ለስደት መዳረጋቸውን ለማረጋገጥ ችለናል።
ተሰዳጆቹ ጋዜጠኞች
1፣ ቶማስ አያሌው (የአፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ማኔጂንግ ዳይሬክተር)፣
2፣ ግዛው ታዬ (የሎሚ መጽሔት አሳታሚ እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር)፣
3፣ ዳንኤል ድርሻ (የሎሚ መጽሔት ሚዲያ ዳይሬክተር)፣
4፣ ሰናይ አባተ ቸርነት (የሎሚ መጽሔት ዋና አዘጋጅ)፣
5፣ አቦነሽ አበራ (የሎሚ መጽሔት ከፍተኛ ሪፖርተር)፣
6፣ ሰብለወንጌል መከተ (የሎሚ መጽሔት ከፍተኛ ሪፖርተር)፣
7፣ እንዳልካቸው ተስፋዬ (የአዲስ ጉዳይ መጽሔት አሳታሚ)፣
8፣ ኢብራሂም ሻፊ (የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ምክትል ዋና አዘጋጅ)፣
9፣ እንዳለ ተሼ (የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ከፍተኛ አዘጋጅ)፣
10፣ ሃብታሙ ስዩም (የአዲስ ጉዳይ አዘጋጅና አምደኛ) እና
11፣ አስናቀ ልባዊ (የጃኖ መጽሔት አሳታሚ እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር)
12፣ ዳዊት ሰለሞን (ፍኖተ ነፃነት) ናቸው።
ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት በደረሰባቸው ወከባ፣ እንግልት፣ ማስፈራራት፣ የቢሮ መታሸግ እንዲሁም ፍትህ ሚኒስቴር በመሰረተባቸው ክስ እስከ አስራ ስድስት ዓመት በእስር ሊቆዩ እንደሚችሉ በመረዳታቸው መሆኑን ለመረዳት ችለናል።
ለነፃው ፕሬስ ቅርብ የሆኑ ወገኖች ገዥው ፓርቲ በፃው ፕሬስ ላይ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚያካሂደውን ወከባ እያወገዙ ይገኛሉ። ላለፉት አራት ወራት በእስር ላይ የሚገኙትና በሽብርተኝነት የተከሰሱትን ሦስት ጋዜጠኞችና ስድስት ብሎገሮችን ተከትሎ በስድስት የሕትመት ውጤቶች ላይ የተመሰረተውን ክስ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ዛሬ ዜና አጠናካሪ ለነዚሁ ወገኖች ላቀረበላቸው ጥያቄ፤ “በሚቀጥለው ዓመት (2007 ዓ.ም.) ለሚካሄደው ምርጫ ገዥው ፓርቲ የያዘው የቅድመ ምርጫ የጽዳት ዘመቻ ነው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=1459#sthash.ymZ5EKrB.TGIeXtJf.dpuf

ESAT Breaking news EPPF,G7 ETAL agreed to form Unity | ESATTUBE

ESAT Breaking news EPPF,G7 ETAL agreed to form Unity | ESATTUBE

Friday, 22 August 2014

አብርሃ ደስታ ሃብታሙ አያሌዉና እና ኤርትራ ( ግርማ ካሳ)


ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራ ድርጅት ጋር እና ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በመገናኘት ፤ እንዲሁም ከባንክ በትዕዛዝ ብር በመቀበል የግንቦት 7 ተልዕኮና አላማ ለመፈፀም፤ ቁጥራቸው ከ60 በላይ የሆኑ ግለሰቦችን ለዚህ ጥፋት እንዲሰማሩ በማድረግ» የሚል ክስ ነው በወዲ ሃዉዜን/ትግራይ በሆነው አንጋፋ ፖለቲከኛ እና ብሎገር ላይ ክስ የቀረበው። ሌላው አንጋፋና አንደበተ ርትኡ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ ግብረ ኃይል ሰብሳቢ፣ ሃብታሙ አያሌውም፣ «የግንቦት ሰባት ተባባሪ ነው» በሚል ነው ለመክሰስ ነው ዝግጅት እየተደረገ ያለው።
አብርሃ ደስታ እና ሃብታሙ አያሌው ፣ «ግንቦት ሰባትን ይደግፋሉ» የሚል ክስ ከቀረበባቸው፣ በተዘዋዋሪ መንገድ «ከሻእቢያ ጋር ወዳጆች ናቸው» ማለት ነው። ታዲያ የሻእቢያ ወዳጅ የሆነ ሰው፣ የኤርትራን መገንጠል ተቃዉሞ፣ ወይንም የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት መከበር እንዳለበት በማስመር ይናገራል ወይ ? እስቲ የጸረ-ሽብርና የአገር ደህንነት ተብዬው ምላሽ ይስጠን !!!
ሁላችንም እንደምናውቀው፣ በኤርትራ በኩል ትግል እናደርጋለን የሚሉ ወገኖች፣ ኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት ሊናገሩ አይችሉም። በሻእቢያ ሥር እስካሉ ድረስ ቀይ መስመር ተሰምሮላቸዋል። እነ ግንቦት ሰባቶች፣ ኦነጎች …፣ እርዳታ የሚያገኙጥ ከሻእቢያ ማእከላቼ ደግሞ አስመራ እስከሆነ ድረስ፣ «ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል» ብለው የመናገራቸው ነገር ጭራሽ የማይታሰብ ነው።
ዶር ብርሃኑ ነጋ ከቃሊት እሥር ቤት ሆነው የጻፉት አንድ መጽሃፍ ነበር። መጽሀፍ ላይ ባለው የ ኤርትራ ካርታ ፣ ኤርትራ ተቆርጣለች። ሃብታሙ አያሌው የጻፈው መጽሃፍ ላይ በሚታየው የ ኤርትር ካርታ ኤርትራ አልተቆረጠችም። ሃብታሙ አያሌው፣ ምንም እንኳን ሻእቢያና ሕወሃት/ኢሕአዴግ ከመረብ በስተሰሜን እና በስተደቡብ ያለዉን ሕዝብ ከፋፍለው፣ በደም ቢያቃቡትም፣ «ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ሁለቱም ወገኖች አሸናፊ በሆኑበት መልኩ፣ ወንድማማቾችን አንድ ማድረግ ይቻላል» የሚል እምነት ስላለው ነው፣ ኤርትራ ከተቀረው የኢትዮጵያ አካል ጋር የቀላቀላት። ከ23 አመታት በፊት ያለው አስቦ ሳይሆን ፣ ወደፊት የሚሆነው ታይቶት ነው። ታዲያ ይህ አይነት ፖለቲከኛ ነው የሻእቢያ አሽከር ነው ተብሎ የሚከሰሰው ?
ወደ አብርሃ ደስታ ልውሰዳችሁ። በቅርብ ጊዜ ስለ አሰብ የጻፈው አስደናቂ ጽሁፍ ነበር። «ጦርነት ፈርተን ግን ሐገራችንን አሳልፈን አንሰጥም» በሚል ርእስ፣ በአደብ ጉዳይ ላይ፣ አብርሃ ደስታ ሲጸፍ « እኛ ጦርነት አንፈልግም። ሕጋዊ ንብረታችን (ወደባችን) በሰለማዊ መንገድ እንዲሰጠን ነው የምንጠይቀው። አዎ! ጦርነት አንፈልግም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ግን ጦርነት ከፍተን በሃይል የሌላ ሀገርና ህዝብ ንብረት አንወርም ማለት እንጂ ጦርነት ፈርተን ልአላዊ ግዛታችን (ሃብታችን) ለሌሎች ሃይሎች አሳልፈን እንሰጣለን ማለት አይደለም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ጦርነት እንፈራለን ማለት አይደለም። አዎ! ጦርነት ስለማንፈልግ ሌሎች ህዝቦችን አንወርም። ጦርነት ፈርተን ግን እናት ሀገራችን አናስደፍርም» ነበር ያለው።
ታዲያ በምን መሰፍርትና ሚዛን ነው አቶ ሃብታሙ አያሌው እና አቶ አብርሃ ደስታ የ«ሻእቢያ ተላላኪ» የሚሆኑት ? በምን መስፈርት ነው ግንቦት ሰባቶች ሊባሉ የቻሉት ?
«ህወሓት በራሱ ኮ የሻዕቢያ ተልእኮ ለማስፈፀም በሻዕቢያ የተቋቋመ ድርጅት ነው። ህወሓት የመሰረተው ማነው? ሻዕቢያ ነው። ሻዕቢያ መሓሪ ተኽለ (ሙሴ) የተባለ ኤርትራዊ የሻዕቢያ አባል በትግራይ ለሻዕቢያ ሊያግዝ የሚችል ድርጅት እንዲያቋቁም ወደ ኢትዮዽያ ላከ። እነዚህ ህወሓት የመሰረቱ የሚባሉ ሰባት ሰዎች አሰባስቦ እንዲደራጁ አደረገ» ብሎ አብርሃ ደስታ እንደጻፈው፣ ለሻእቢያ ዉስጥ ዉስጡን የሚቆረቀረዉስ ሕወሃት አይደለችንም ? ያ ባይሆን ኖሮ ተሽቀዳድሞ የአልጀርስ ስምምነት ይፈረም ነበርን? ያ ባይሆን ኖሮ አገር ቤት ካሉ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ጋር አልነጋገርም እያሉ፣ የሕወሃት/ኢሕአዴጉ ዳግማዊ መለስ ዜናዊ፣ ኃይለማሪያም ደሳለኝ «ካስፈለገም አስመራ ድረስ እሄዳለሁ» ይሉ ነበርን ?
እርግጥ ነው እነዚህ ሁለቱ አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኞች፣ ኢሳት በተሰኘው ሜዲያ ቀርበው ቃለ ምልልስ አድርገዋል። አቦይ ስብሐት ነጋ፣ አምባሳደር ቪኪ ሃደልሰን፣ ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን፣ ወንጌላዊ ዳንኤል ጣሰው ..የመሳሰሉትም በኢሳት ቀርበዋል። ታዲያ እነ አባይ ስብሐት ፣ «ኢሳት ላይ ቀረባችሁ» ተብለው ወደ ወህኒ የወረዱበት ሁኔታስ የታለ ?
በአንድ ሜዲያ መቅረብ አንድን ሰው ጥፋተኛ አያሰኘዉም። አንድ ሰው መከሰስ ካለበት፣ ሊከሰስ የሚገባው በቃለ መጠይቆቹ ዉስጥ ባለው ይዘት ነው። አቶ ሃብታሙና አቶ አብርሃ፣ ሲጽፉም ሲናገሩም በግልጽና በአደባባይ እንደመሆኑ «ይሄን ተናገረዋል.. » ተብለው የሚከሰሱበት ነጥብ ይኖራል ብዬ አላስብም። በመሆኑም አገዛዙ ፣ እነዚህ ሰላማዊ ዜጎችን ሽብርተኞች ናቸው ብሎ ማሰሩ የትም አያደርሰውም። ይህ አይነቱ ፍርድ ገምድልነትና ዜጎችን ያለ ከልካይ ማሰርና ማንገላታት መቆም አለበት።






Friday, 15 August 2014

Ethiopia - Bloggers and human rights

                             

Ethiopia - Bloggers and human rights defenders held for more then 100 days and charged with treason for using free software


Joint statement by Front Line Defenders and Tactical Technology Collective on arrest of Zone9 bloggers: In the recentZone9 Bloggers case in Ethiopia the authorities have fabricated charges of destabilising the nation and terrorism in an attempt to silence any independent voices talking about the human rights situation in the country.
Part of the supposed evidence they have presented to try to substantiate the charges is that the human rights defenders used some of the tools and tactics contained in the Security in-a-boxpackage which is publicly available on the Internet.



Security in-a-box is a collaborative project developed by Front Line Defenders and the Tactical Technology Collective. It was created to meet the digital security and privacy needs of advocates and human rights defenders to enable them to communicate securely online.
Security in-a-box includes a How-to Booklet, which addresses a number of important digital security issues. It also provides a collection of Hands-on Guides, each of which includes a particular freeware or open source software tool, as well as instructions on how you can use that tool to secure your computer, protect your information or maintain the privacy of your Internet communication.
The content of Security in-a-box is entirely legitimate, the software is all publicly available for free, and its use is consistent with international human rights law. The Ethiopian authorities have falsely suggested that the legitimate concerns of the human rights defenders about the privacy of their information and communications is evidence of inciting violence or seeking to overthrow the government.
Background
On 17 July 2014, the Ethiopian authorities formally charged ten human rights defenders and bloggers under anti-terrorism legislation. Seven of those charged are members of Zone9, while three others are independent journalists. With the exception of Soliana Shimelis, who was charged in absentia, the other six Zone9 members Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Befekadu Hailu, Atnaf Birhane, Zelalem Kibret and Abel Wabela, as well as journalists Tesfalem WaldyesEdom Kassaye, and Asmamaw Hailegiorgishave been in detention since 25 April 2014.
Zone9 is a group of bloggers and human rights defenders who discuss online issues of public interest in Ethiopia. Soliana Shimelis and her fellow bloggers are accused of having links to two Ethiopian groups, Ginbot 7 and the Oromo Liberation Front (OLF), which have been labelled “terrorist organisations” by the Ethiopian government since 2011.
Before these formal charges were brought on 17 July 2014, human rights defenders Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Befekadu Hailu, Atnaf Birhane, Zelalem Kibret, Abel Wabela, Tesfalem Waldyes, Edom Kassaye, and Asmamaw Hailegiorgis had been detained for over 80 days, which is the limit of detention without charge in Ethiopian law. They are accused of intending to “destabilise the nation” and of using their blogging as a cover for unlawful activities. Reportedly, human rights defender Natnael Feleke was accused of receiving cash, estimated at Birr 48,000 (about €1,780), from Ginbot7 for the purpose of inciting violence. The other bloggers are accused of receiving orders from Ginbot7 and OLF and of being part of a plan to organise terrorist acts and overthrow the government by force.
Soliana Shimelis has been accused of founding Zone9, co-ordinating communications between Zone9 and Ginbot7, and organising a security training for fellow bloggers using the ad hoc human rights training tool “NGO Security in a Box”, which is available online.
Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Befekadu Hailu, Atnaf Birhane, Zelalem Kibret, Abel Wabela, Tesfalem Waldyes, Edom Kassaye, and Asmamaw Hailegiorgis were all arrested during an operation launched by the Ethiopian police on 25 April 2014. This came just two days after Zone9 had announced that it would resume blogging after suspending its activities for approximately six months due to a series of threats against their members. Soliana Shimelis was charged in absentia and is not currently in custody.
Front Line Defenders and Tactical Technology Collective are concerned about the fact that these bloggers had been in detention without charge beyond the legal limits, in connection with their legitimate work in defence of human rights, and are further concerned by the targeting of human rights defenders in Ethiopia on the basis of alleged connections with “terrorist organisations”.
                       

አሳፋሪው የVOA ቅሌት

ወያኔ ሕወሓት

ወያኔ ሕወሓት በቅርቡ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ ተጨመረ ብሎ በኢቲቪ ሲደሶኩርና ብሎም የተጨመረ ዶሞዝ ከእድገቱ የሚመጣጠን መሆኑን ኣፅንኦት ሰጥቶ ሲለፈልፍ ነበር የከረመው!!! እዉነቱ ግን የሓላ ሓላ ብቅ ብሎ የተጨመረ ዶሞዝ እንዳየነው ሲሆን ማፍያው ወያኔ በደሞዝ ጭማሪ ለይ የሚከተሉትን ኣራት ድራማዎች ኣሳይቶናል!!!
1. ዶሞዝ ጨመርኩኝ ብሎ ሲል ታክስ 35% ኣስገብቶ ከመንግስት ሰራተኛ ኪስ መዝረፍ ጀመረ ! የተጨመረው ደሞዝ የታክስ መጠኑ በማሳደግ ድሮ ከነበረው 32% ኣሁን 3% በመጨመር ምርጥ ድርማን ሰርቶዋል
2. ከሃገሪቱ ፈጣን እድገት የሚመጣጠን ነው እያለ ሲደሶኩር የከረመው ዝቅተኛ የደሞዝ ጭማሪ 200 ብር ሲሆን 4000 ይከፈል የነበረው ደግሞ በ33% ተባዝቶ ኣሁን 1320 ብር ጨምሮዋል!!! እዚጋ የሚታየው ጉዳይ በዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይና በደህና ተከፋይ የኑሮ ዉድነት ከማዛመት በስተቀር የደሞዝ ጭማሪው ለዜና መሳርያ ብቻ እንደሆነ ለማወቅ ወያኔ በቻ ኣለመሆን በቂ ነው ( ኮካዎች ቁጥር ፎብያ ስላላቸው ነው)!!!
3. ይህ የፈጣን እድገት የደሞዝ ጭማሪ የሃገሪቱ ነባራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ደረጃም ወያኔዎች ሳያቁት የት እንዳለንም ጭምር ኣሳይቶናል!!! በፈጣን እድገት ያለች ሃገር የደሞዝ ጭማሪ 200 ብር ስታደርግ እነ ሕወሓት ሓቁን ሳይታወቅባቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ ማሳየታቸው ህዝብ ማወቅ ችሎዋል!!!
4. መከረኛው ነጋዴ ንሮ ለማስወደድ በበርበሬ በዘይት በስካር ወዘተ የምግብ ኣገልግሎት የሚዉሉ እቃዎች ላይ ዋጋ ጨመራቹ ኣልጨመራችሁ እያለ የሌባና ፖሊስ ጨዋታ ወደ መጫወት ሰተት ብሎ ገብቶዋል!!!! ከዉሸት ወጥተው ኮካዎች የሃገሪቱ ትክክለኛ ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደማይችሉት የሚያዉቁ ሕወሓቶች ዛሬ በነጋዴ ላይ መንግስትና ህዝብ ለመለያያት ወዘተ እያሉ በመከራ ኑሮዉን ለማሸነፍ እየተታገለ ላለው ህዝበ የስራ ቦታው ማሸግ እንደ መፍትሔ ተያይዞዉታል... ኣንጀትየ መንግስት!!!
ባጠቃለይ ሕወሓት እችን ሓገር ከመዝረፍ የዘለለ ፖሊሲ እንደሌለው 23 ዓመታት በሙሉ በዉሸት ስልጣን ላይ እንደኖረ ህዝባችን ኣዉቆ ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ወያኔን ቀብረን በኢትዮጵያ ሃገራችን ባንዴራችንን ከፍ ኣድርገን የምንኖርባት ኢትዮጵያ እዉን ለመሆን 1 ዓመት ብቻ ቀርቶናል!!! (ግንቦት 2007 ዓም)
ነፃነት ቀርባለችና ... ወደ ሃላ ማየት የለም!!!!

Thursday, 14 August 2014

የአዲስ አበባ መስተዳድር

የአዲስ አበባ መስተዳድር በቤቶች ግንባታ ዙሪያ ለምርጫ እንዲደርስ በሚል አስቸኳይ ትእዛዝ ሰጠ
በ40 በ60 በሚባለው የቤቶች መርሃግብር የታቀፉ የዲያስፖራ አባላት ከቀጣዩ ዓመት ምርጫ በፊት ቤት እንዲሰጣቸው የአዲስ አበባ መስተዳድር መመሪያ መስጠቱ ታውቋል።
ሆኖም የጠቅላላ ተመዝጋቢውን የቤት ፍላጎት ለመሸፈን በትንሹ ከ16 ዓመታት በላይ ጊዜን እንደሚወስድ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
የአዲስ አበባ ቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ እስካሁን 13ሺህ 800 ቤቶችን በሰንጋተራ እና ቃሊቲ ክራውን ሆቴል በመሳሰሉ አካባቢዎች ላይ እየገነባ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ፣ እነዚህን ቤቶች እስከሚቀጥለው ዓመት አጋማሽ ድረስ ለዕድለኞች ለማስተላለፍ ታቅዷል።
የአስተዳደሩ ምንጮች እንደገለጹት ቤቶቹ ከቀጣይ ዓመት ምርጫ በፊት ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው እንዲተላለፉ ከአስተዳደሩ መመሪያ ተሰጥቷል። ሆኖም ለ40 በ60 የቤቶች ፕሮግራም የተመዘገበው ጠቅላላ ሕዝብ ቁጥር 164 ሺህ 779 ያህል ሲሆን አስተዳደሩ ግን በዓመት ከ10 ሺህ ቤቶች በላይ ቤቶችን የመገንባት አቅም ባለመፍጠሩ የተመዘገቡትን ብቻ ለማዳረስ ከ16 ዓመታት በላይ ጊዜን እንደሚፈልግ የአስተዳደሩ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
ይህ ደግሞ ከዛሬ ነገ የመኖሪያ ቤት ባለቤት እሆናለሁ ብሎ ተስፋ ላደረገው ሕዝብ ተስፋ አስቆራጭ ዜና ነው ብለዋል፡፡
በ20/80 በተለምዶ ኮንዶሚኒየም ፕሮግራም የምርጫ 97 ን መቃረብ ታሳቢ አድርጎ ሲጀመር ከ350ሺ በላይ የአዲስአበባ ነዋሪ መኖሪያ ቤት እፈልጋለሁ ብሎ መመዝገቡን ያስታወሱት ምንጮቹ ፣ ፕሮግራሙ 10 ዓመታት ያህል ቆይቶ መመለስ የቻለው ግን 100 ሺ በታች ቤት ፈላጊዎችን ጥያቄ ነው ብለዋል፡፡ በዚህ መረጃ መሠረት የጠቅላላ ተመዝጋቢውን ፍላጎት ለሟሟላት ተጨማሪ ከ20 ዓመታት በላይ ጊዜን እንደሚወስድ አፈጻጸሙ በራሱ የሚናገር ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡
የአስተዳደሩ ምንጭ እንደሚሉት መንግሥት በአዲስ አበባ በዓመት ለቤቶች ግንባታ ብቻ ከ2 እስከ 3 ቢሊየን ብር እያወጣ መሆኑን አስታውሰው ከዚህ በላይ ለማውጣት የፋይናንስ አቅም ችግር መኖሩን፣ ገንዘቡ ቢገኝም በግንባታ አፈጻጸም በኩል የአቅም ችግር በመኖሩ በአጭር ጊዜ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትን ለመመለስ የማይችልበት አጣብቂኝ ውስጥ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም እንደገለጹት ደግሞ ዲያስፖራው በፈለገበት አካባቢ ቤት ለመስራት ይችል ዘንድ ክልሎች መመሪያ እንዲያወጡ መታዘዙን ገልጸዋል። ሁሉም ክልሎች ተመሳሳይ የሆነ መመሪያ ባለማውጣታቸው ለዲያስፖራው ቤት ለማደል የታቀደው እቅድ የተፈለገውን ውጤት አለማምጣቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጅ ኢሳት የአዲስ አበባን አዲሱን ካርታ ዝግጅት አስመልክቶ ከወራት በፊት በሰራው ዘገባ፣ የቤት ግንባታ መርሃግብሩ የተሰናከለው በአዲስ አበባ የቤት መስሪያ ባዶ ቦታ በመጥፋቱ ነው። ቀደም ብሎ የኦሮምያን ልዩ ዞኖች ወደ አዲስ አበባ በመጠቅለል የቤት መስሪያ ቦታዎችን ለማግኘት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ የኦሮምያ ክልል አንዳንድ ባለስልጣናትና አብዛኛው የኦሮሞ ተወላጅ በመቃወሙ እቅዱን በቀላሉ ተግባራዊ ማድረግ አልተቻለም። ዲያስፖራው ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ ቦታዎችን እንዲጠይቅ ለማግባባት ኢምባሲዎች የስራ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ለአባይ ግድብ በቦንድ ስም ገንዘብ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ገንዘብ ለማሰባሰብ የታቀደው እቅድ አለመሳካቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምነዋል። ከፍተኛ ገንዘብ ይገኝበታል የተባለው የአሜሪካ የቦንድ ሽያጭ አምና ጭራሽ አልተካሄደም ብሎ መናገር እንደሚቻል ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በሁሉም አገሮች ያለው የቦንድ ሽያጭ ደካማ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ፣ ለድክምቱ ዝርዝር ምክንያቶችን አላቀረቡም። የዶ/ር ቴዎድሮስ ገለጻ፣ ኢሳት ከዚህ ቀደም የቦንድ ሽያጩ በውጭ አገር አለመሳካቱን ሲዘግብ የቆየውን ያረጋገጠ ሆኗል።
በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ገንዘብ ለመሰብሰብ በገዢው ፓርቲ በኩል የሚዘጋጁትን ዝግጅቶች አጥብቆ ሲቃወም እንደነበር ይታወቃል። አቶ መለስ የአባይን ግድብ እቅድ ይፋ ሲያደርጉ በውጭ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ 1 ቢሊዮን ዶላር ያዋጣል የሚል እምነት ነበራቸው፣ ይሁን እንጅ እስካሁን ባለው መረጃ በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ከ20 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሊያዋጣ አልቻለም።

Monday, 11 August 2014

ደጋፊዎችን የማሰባሰብ ጥረት


የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በህሊናና የፓለቲካ እስረኞች ሁሉ ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ መክበድ፤ በፀረ-ሽብርተኝነት ስም በሕዝብ ላይ የሚነዛው ወያኔያዊ ሽብር መብዛት፤ እስሩ፣ እንግልቱ፣ መሳደዱ፣ የሀብት ዘረፋው በየዕለቱ እየጨመረ መምጣት እና ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኑሮ እየከበደ መምጣቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ጋር ወሳኝ የሆነ ትግል መግጠሚያ ወቅት ላይ መደረሱ አመላካች ሆኗል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ የትግል መንፈስ መነሳሳት በተጨባጭ ከሚያረጋግጡ አመላካቾች አንዱ የግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አባል ለመሆኑ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን መጨመር ነው። ይህንን ለውጥ ተከትሎም ግንቦት 7 የአባላት ቅበላን ሥራ ለማፋጠን የሚረዱ እርምጃዎች ወስዷል። ሆኖም ግን በአባላት ቅበላ ወቅት ሊታለፉ የማይችሉ ጥንቃቄዎች መኖር እንዳለባቸው ደጋፊዎችም እጩ አባላትም ይረዳሉ ተብሎ ይታመናል።
በዚህም ምክንያት አሁንም እየጨመረ የመጣን ንቅናቄውን የመቀላቀል ፍላጎትን ለማስተናገድ፤ ለተግባራዊ ሥራዎች የተነሳሱ፣ ዓላማችንና ንቅናቄዓችንን የሚደግፉ ሆኖም ግን በተለያዩ ምክንያቶች በድርጅት አባልነት መቀላቀል የማይችሉ ወይም የማይፈልጉ አባላትን ለማሳተፍ የሚረዳ መዋቅር ማዘጋጀት ተገቢ መሆኑ ታምኖበታል። ስለሆነም እነዚህን ወገኖቻችን የትግላችን አካል ብቻ ሳይሆን የንቅናቄዓችንም አካል ለማድረግ እንዲቻል በአባላት ጉዳይ ሥር የደጋፊዎች ማስተባበሪያ መዋቅር እንዲደራጅ ተደርጓል። ይህ አደራጀት ግንቦት 7ን ለማዘመን እና ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ የተመቸ ድርጅት ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አካል ነው። ይህ አደረጃጀት በአንድ በኩል የድርጅቱን ምስጢራዊት ለመጠበቅ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ ባሉ ፍላጎቶች መካከል ያለውን ቅራኔ ለመቅረፍ የቀረበ መፍትሔ ነው።
በዚህም መሠረት በአባልነት ለመመዝገብ ስለእናንተ ምስክርነት መስጠት የሚችል የግንቦት 7 አባል ማቅረብ ለጊዜው ያልቻላችሁ፤ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት የግንቦት 7 ደጋፊ እንጂ አባል መሆን የማትፈልጉ ወገኖቻችን ግንቦት 7 ፍላጎታችሁን የሚያሟላ መዋቅር ማዘጋጀቱን በይፋ ያበስራል።
የግንቦት 7 ደጋፊ በግንቦት 7 የውስጥ ጉዳዮች የመወሰን፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት አይኑረው እንጂ የንቅናቄው ሙሉ ተሳታፊና ባለቤት በመሆኑ በልበ ሙሉነት “እኔም ግንቦት 7 ነኝ” ማለት ይችላል። የግንቦት 7 ደጋፊ እንደማንኛውም አባል ድርጅታዊ ሥራዎች ሊሰጡት ይችላል።
በደጋፊነት ለመመዝገብ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ኢሜል፣ እድሜ፣ ጾታ፣ ከተማና የሚኖርበት ሀገር ብቻ የሚጠይቅ የድህረ ገጽ ቅጽ መሙላት ያስፈልጋል። ይህ ቅጽ በንቅናቄው ድህረ ገጽ ላይ ይገኛል። ደጋፊዎች እውነተኛ ስማቸውን የመስጠት ግዴታ የለባቸውም። አንድ ደጋፊ በየወሩ የሚፈቅደውንና የሚችለውን ያህል ገንዘብ እንደሚያዋጣ ይጠበቅበታል፤ ይህ የደጋፊነቱ አንዱ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል። ደጋፊ በሚኖርበት ከተማ በሚደረጉ የትግል እንቅስቃሴዎች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ይጠበቅበታል፤ ይህም ሌላው የደጋፊነት መገለጫ ነው። ደጋፊዎች የንቅናቄው ሳምንታዊ ጋዜጣና ወርሃዊ ልዩ መልዕክት በግል ኢሜላቸው እንዲደርሳቸው ይደረጋል። ደጋፊዎች በተግባር በሚያሳዩት ተሳትፎ ከአባላት ጋር ቅርርብ በመፍጠር ወደ ከደጋፊነት ወደ አባልነት የሚሸጋገሩትን መንገድ ያመቻችላቸዋል።
በተለያዩ ምክንያቶች ራሳችሁን በህወሓትና ጀሌዎቹ መዋቅር ውስጥ ያገኛችሁና በወያኔ እኩይ ተግባራት የህሊና እረፍት ያጣችሁ የሕዝብ ወገኖች ይህንን መዋቅር ከግንቦት 7 ጋር በምስጢር ለመገናኛነት ተጠቀሙበት። በመከላከያና በፓሊስ እንዲሁም በራሱ በኢሕአዴግ ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ይህንን መስመር በግኑኝነት መመስረቻነት ተጠቀሙበት። በወያኔ የስለላ ወዋቅር ውስጥ ያላችሁም እድሉን ተጠቀሙበት።
በድህረ ገጻችን ላይ http://www.ginbot7.org/supporter-form/ በቀጥታ በመመዝገብ የግንቦት 7 ደጋፊ መሆን ይቻላል። ድረገጹ በማይከፈትባቸው ቦታዎች በ supporter@ginbot7.org ይፃፉ።






Friday, 1 August 2014

የግንቦት 7 ወቅታዊ መልዕክት፡ የህወሃት ሽብር መቆም አለበት!

ዛሬ በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለ አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎችን በፖለቲካ አመለካከታቸው፣ መንግስት በመተቸታቸው በግልጽ በመጻፋቸውና በአደባባይ በመናገራቸው ከዚህም አልፎ በጥርጣሬ በተለይም በብሄረሰብ ማንነታቸው እያሳደደ የሚያፍን የሚያሰቃይና የሚገል የሽብር ተቋም ካለ ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ መሬት ላይ ሰላማዊ ዜጎችን ኢላማ ያደረገ የተቃውሞ ሃይል በተግባርም ሆነ በአስተሳሰብ ከወያኔ ውጪ አንዳች ሃይል የለም።


                                      Ginbot_7_Logo_L

አፋኙ የወያኔ ስርአት በተለየም የህዝቡን ሀብትና ንብረት እየዘረፉ የሚቀማጠሉት የህወሃት መሪዎችና ሎሌዎቻቸው የተቃውሞ ድምጽ በሰሙ ቁጥር እንደሚሸበሩና እንቅልፍ አጥተው እንደሚያድሩ ይታወቃል። አፍነውና ዘርፈው ገለው የሚገዙት ህዝብ ግፍ በዛብኝ ብሎ በተናገረ ቁጥር የሚሸበሩት እነሱ ብቻ እንጂ ህዝቡ አይደለም።
በኢትዮጵያ ምድር ያለው አሸባሪ ወያኔ ብቻ መሆኑን ሺ ምሳሌዎችን ጠቅሶ ማስረዳት ይቻላል። ሶስት አመት ሙሉ የሰላም እጃቸውን እየዘረጉ ከልመና ባልተለየ ሁኔታ መብታቸውን የጠየቁና ድምጻችን ይሰማ ያሉት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማንንም ዜጋ አላሸበሩም። የተገላቢጦሽ እነሱ አሸባሪ ተብለው የግፍ ሰቆቃ ይፈጸምባቸዋል። ጋዜጠኞችና ጦማሪዎቹ መንግስት ያወጣውን ህግ እንዲያከብር ስለጠየቁ በአደባባይ ስለጻፉ ግፍ ይፈጸምባቸዋል። እነሱ ያሸበሩት ሀገርና ህዝብ የለም። ከመንገድ ላይ ጎትተው እንደ እባብ ቀጥቅጠውና ፈነካክተው በማግስቱ ፍርድ ቤት ያቀረቧት ወየንሸት ሞላ የተባለች ባለ ተስፋ ወጣት የወያኔ አረመኔዎች በሙስሊሙ ህዝብ ላይ የሚሰሩትን ጭፍጨፋ እግር ጥሏት ከማየትና ከመታዘብ ውጪ ያሸበረችው ሰው፣ ሀገር የለም። በየወህኒ ቤቱ እና አፈና ጣቢያው ታስረው የሚቀጠቀጡት የኦሮሞ ልጆች ለጥያቄያቸው መልስ ሲጠብቁ ከመጨፍጨፍ ያለፈ የፈጸሙት እብሪት የለም። በየክልሉ ቀና ብለህ ባለስልጣን ተናገርክ፣ ጥያቄ ጠየቅክ፣ ባለስልጣን ደፈርክ፣ ተሰብስበህ አየንህ ወዘተ እየተባለ የሚገረፈው እንደ እንስሳ እየተገደለ የሚጣለው ገበሬ የሰራው ወንጀል የለም። አሸባሪም አይደለም! በየቦታው ቦንብ እየቀበረ አፈንድቶ ንጹሃንን ገድሎ ሊያፈነዱ ሲሉ ፈንድቶባቸው ራሳቸውን ገደሉ ብሎ በአደባባይ የሚሳለቀው አሸባሪው ህወሃት እንጂ ንጹሃኑ አይደለም።
የኛ መሪ አንዳርጋቸው ከልጅነት እድሜው ጀምሮ ራሱን ለህዝብ ነጻነት የሰጠ አርበኛ እንጂ አሸባሪ አይደለም። በተመሳሳይ ውንብድና ከጎረቤት ሀገር ድረስ በአለም አቀፍ የወረበሎች ውንብድና መንገድ ወያኔ እያፈነ የገደላቸው አሮሞዎችና፣ ሱማሌዎች፣ አኙዋኮች፣ አማሮችና ሌሎችም ነጻነት ከመፈለግ ውጪ ያሸበሩት ህዝብና ሀገር የለም።
በኢትዮጵያ ምድር የነጻነት ድምጽና ኮሽታ በሰማ ቁጥር የሚሸበረው ህወሃትና በለሟሎች ብቻ ናቸው። ይህ የነጻነት ድምጽ ደግሞ እየጎላ መሄዱ የማይቀር ነውና ወያኔ ሰፈር ሽብር ይሆናል።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወጣት፣ ሴት፣ ሽማግሌ፣ ገበሬ እና በየቦታው ያላችሁ የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ! አሸባሪህ ወያኔና ወያኔ ብቻ መሆኑን አውቀህ በገዛ ሀገርህ ላይ ነጻነት በተመኘህና በጠየቅህ ጊዜ ሁሉ ለሽብር ጥቃቱ ኢላማ ያደረጉህን ወያኔ ተባብረን ከላያችን ለማውረድ ተነስ! በያለህበት እምቢ በል! ለወያኔ የሚጠቅም የመሰለህን ነገር ሁሉ አታድርግ! አትተባበር! ሸቀጣቸውን አትግዛ! ወያኔዎችን ከማህበራዊ ሂወትህ አግል! የቻልክ ሁሉ ደግሞ የነጻነት አርበኞችን ዛሬ ነገ ሳትል አሁን ተቀላቀል!!! ነጻነታችን ያለው በእጃችን ላይ መሆኑን አትዘንጋ። ግንቦት 7 ሁልጊዜም ከመቼውም ጠንክሮ ከጎንህ ነው።
የወያኔን ሽብር በተባበረ ሃይል እናቁመው!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!